onsdag 19. mars 2014

መንግስት ስለ ጣይቱ ልጆች ጨንቆት ዋለ (Semayawi Party Update)

March 18, 2014
Semayawi Party- Ethiopia (Update)
ምንም የረባ መከራክሪያ ያላቀረበው ፖሊስ መናገር አቅቶት ሲንተባተብ ነው የዋለው በተጨማሪ ሌሎች መያዝ የልቻልናቸው 20 እሩጫው ላይ የነበሩ ሴቶች ስላሉ በማለት የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል ሲጀምር ችሎቱ የታየው በጽ/ቤት ነው የነበረው የሰዉ ብዛት ያስጨነቀው መንግስት ሰዉ በችሎት እንዳይታደም ክርክሩን እንዳይሰማ በጣም ጠባብ በሆነችው ቢሮ ከአቅሙዋ በላይ የሆኑ ተከሳሾችን ለማሰተናገድ ተገዳለች ውሳኔ መስጠት የማይችለው ዳኛ ለነገ መጋቢት 10/2006 በመደበኛ ይታይ በሚል ተልካሻ ምክንያት ቀጥሮአቸዋልየጣይቱ ልጆች ግን በጣም በሚያሰድሰት ሞራልና የትግለ ሰሜት ላይ ሆነው ለማየት ችለናል፡፡
ችሎቱንም ለመከታተል የተለያዩ ሀገራት የኢንባሲ ተወካዮች፤ የሰማያዊ ፓረቲ አባላትና ደጋፊዎች እነዲሁም ጋዜጠኞች ተገኝተዋል
እወነት ሁሌም ታሸንፋለች ሁሌም ከጎናችሁ ነን!!!

fredag 14. mars 2014

በአሜሪካ የሚኖረው የሕወሐት ወንጀለኛ


March 14, 2014

ከኢየሩሳሌም አርአያ
The Ethiopian author, former TPLF torture czar and spymaster “Professor” Bisrat Amare
Bisrat Amare former head of TPLF Intelligence
የሕወሐት አባል የሆነውና በአሜሪካ የሚኖረው ብስራት አማረ በርካታ ወንጀሎችን እንደፈፀመ የቅርብ ምንጮች አጋለጡ። ሕወሐት በረሃ እያለ የባዶ 6 እስር ቤት ዋና ሃላፊ የነበረው ብስራት አማረ የኢ.ህ.አ.ፓ አባላት የነበሩት እነ ፀጋዬ ገ/መድህን (ደብተራው) ጨምሮ በሕወሐት የተያዙትን በሙሉ ወረኢ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ በነበረ እስር ቤት በጅምላ አሰቃይቶ እንደገደላቸው ምንጮቹ አረጋግጠዋል። በሺህ የሚቆጠሩ የትግራይ ሰዎች « ኢዲዩና ፊውዳል..» በሚል ባዶ 6 ተብሎ ይጠራ በነበረው እስር ቤት ተሰቃይተው እንዲገደሉ የተደረጉት በብስራት አማረ መሆኑን የጠቆሙት ምንጮቹ ከዚህ በተጨማሪ የድርጅቱን በርካታ አባላት እንዳስገደለ አያይዘው ገልፀዋል። እነተክሉ ሃዋዝ በዚህ ወንጀለኛ ከተገደሉት ይጠቀሳሉ ሲሉ ያክላሉ። 
በ1983ዓ.ም ሕወሐት/ኢህአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላ የሟቹ የደህንነት ሹም ክንፈ ገ/መድህን ምክትል የነበረው ብስራት አማረ ከቤተ መንግስት የጃንሆይ የነበረ ከፍተኛ ወርቅ በመዝረፍ መውሰዱን ያጋለጡት ምንጮቹ በዚህ የዘረፋ ወንጀል ሆለታ እስር ቤት እንዲገባ መደረጉን ያመለክታሉ። በነስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ትእዛዝ እንዲፈታ ተደርጐ ወደ አሜሪካ የተሸኘው ብስራት አሜሪካ ሲጓዝ የዘረፈውን ወርቅ ይዞ እንደነበረ ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ምንጮች በግርምት ይገልፃሉ። ብስራት አማረ አሜሪካ ከመጣ በኋላ ቅርስ የሆኑትንና የዘረፋቸውን ወርቆች መሸጡንና አንዲት ሴት ለማሻሻጥ የተቀበለችውን 1ኪሎ ወርቅ ከወሰደች በኋላ እንደካደችው ማወቅ ተችሎዋል። ብስራት አማረ ስለዚሁ ጉዳይ ተበሳጭቶ የነገራቸው ምንጮች ማረጋገጫ ይሰጣሉ። የብስራት ታናሽ ወንድም የሆነውና በደህንነት ቢሮ ይሰራ የነበረው ታጋይ ጠስሚ (ጠስሚ -ትርጉሙ ቅቤ ማለት ነው) ከስራው በመልቀቅ የአስመጪና ላኪነት ትልቅ ቢዝነስ መክፈቱን የጠቆሙት ምንጮቹ አክለውም፥ ድርጅቱ የተከፈተው ብስራት አሜሪካ ከገባ በኋላ በላከለት ገንዘብ መሆኑን አስታውቀዋል። (ስለዚሁ ጉዳይ በ1995 ዓ.ም በኢትኦጵ ጋዜጣ መረጃው ይፋ መደረጉና የብስራት ወንድም ቅቤ ኢትኦጵ ቢሮ ድረስ በመምጣት የጋዜጣውን አዘጋጅ በድንጋጤ ተውጦ “የራሴን ቢዝነስ ተቋም ነው፤ እነማን መረጃ እንደሚሰጧችሁ አውቃለሁ። እባካችሁ የእኔንም፣ የወንድሜንም ስም አታንሱ?” በማለት ተማጽኖ አቅርቦ ነበር።) ብስራት አማረ ከሽማግሌው ስብሃት ነጋ ጋር ባለው የጠበቀ ግንኙነት ወደ ኢትዮጵያ ሲመላለስ መቆየቱን ያወሱት ምንጮቹ፣ ወንጀለኛውና ዘራፊው መቀሌ ሄዶ አስገደ ገ/ስላሴን እንደከሰሰ አስታውቀዋል። የደርግ ወንጀለኞች ከአሜሪካ በገዢው ፓርቲ እየተወሰዱ ነገር ግን የኢ.ህ.አ.ፓ አባላትንና ሌሎች ንጹሃን ዜጎችን በጅምላ የፈጀና የአገር ቅርስ የዘረፈ ወንጀለኛ ጠያቂ ማጣቱ አስገራሚ ነው ብለዋል ምንጮቹ። 
ጠያቂ አካል ካለ በወንጀለኛው ብስራት አማረ ላይ ለመመስከር ፈቃደኛ መሆናቸውን አክለዋል። ይህን ምስክርነትና ማረጋገጫ ሊሰጡ የሚችሉና በአሜሪካ የሚኖሩ ሶስት የቀድሞ የሕወሐት ሹሞች እንዳሉና የብስራትን ወንጀል ጠንቅቀው የሚያውቁ መኖራቸውን አያይዘው ጠቁመዋል።

torsdag 13. mars 2014

በዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን ዝክር፤ በእህቶቻችን ኮርተናል!!!


ለዘንድሮው ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን መታሰቢያ በአዲስ አበባ ከተማ በተደረገው የሩጫ ትዕይንት ላይ ወጣት ሴቶች ባሳዩት ልበ ሙሉነት ኮርተናል። የሩጫውን ትዕይንት አስታከው፣ በአብዛኛው የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እንደሆኑ የተነገረላቸው ወጣት ሴቶች ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለህሊና እስረኞች መፈታት እና ለሀገር አንድነት ድምፃቸውን ከፍ አድረገው ጮኸዋል፤ ዘምረዋል። እነዚህ ወጣት ሴቶች በሥርዓቱ ምን ያህል እንደተማረሩ በቃላትም በአካል ንቅናቄም አሳይተዋል። ዘረኛውና ፋሽስቱ ወያኔ ግን “ለምን ተቃወማችሁኝ” ብሎ አስሯቸዋል፤ ከፊሎቹም የደረሱበት አይታወቅም። በእህቶቻችን ቆራጥነት ኮርተናል፤ በወያኔ የፈሪ ዱላ ደግሞ ተቆጥተናል። በ1997 እና 98 “የወላጆቻችን ድምጽ ይከበር” ያሉ ሕፃናትን የጨፈጨፈው ወያኔ በ2006 ወጣት ሴቶችን ከማሰቃየት ይመለሳል ብለን አናምንም። ወያኔ እስካልተወገደ ድረስ የፈሪ ዱላው የማይቀር ነገር ነው።
የወንዶቹን ያህል የተዘገበ አይሁን እንጂ በክፉም በደጉም ሴቶች ያልተሳተፉበት የኢትዮጵያ ታሪክ የለም። የቅርብ ጊዜ ታሪካችንን እንኳን ብናይ በፋሽስት ወረራ ወቅት ኢትዮጵያዊያን ሴቶች በአርበኝነት ዘምተው አዋግተዋል፤ ተዋግተዋል። በተለያዩ ምክንያቶች መዝመት ያልቻሉት ደግሞ በውስጥ አርበኝነት ተሰልፈው የጠላት ምስጢሮች ለአርበኞች እንዲደርሱ በማድረግ ከፍተኛ ጀብዱዎችን ፈጽመዋል። ከፋሺስት ወረራ ወዲህ በነበሩ ዓመታት ውስጥም ለፍትህ እና ለነፃነት በተደረጉ ተጋድሎዎች ሴቶች ጉልህ ተሳትፎ ነበራቸው። በተማሪዎች ትግል ውስጥ ለምሳሌ፣ ወጣት ሴቶች በአመራር ደረጃ በመሳተፍ ትግሉን መርተዋል፤ የሕይወት መስዋዕትነት ጭምር ከፍለዋል። ከዚያ ወዲህም በነበሩት ዓመታት በኢሕአፓ እና ሌሎችም ድርጅቶች አመራርና አባልነት ተሳትፈው ከፍተኛ ተጋድሎ ያደረጉ ኢትዮጵያዊያን ሴቶች ነበሩን። በቅርቡም በምርጫ 97 እንቅስቃሴም የሴቶች በተለይም የወጣት ሴቶች ተሳትፎ ምን ያህል ጉልህ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነውና እናስታውሳለን። ለምርጫ ድምጽ መከበር ወጣት ሽብሬ ደሣለኝን ጨምሮ በርካታ ሴቶች ሕይወታቸውን ሰውተዋል፤ ከዚያ የበለጡት ደግሞ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል። ዛሬም እንደ ርዕዮት ዓለሙ የመሳሰሉ ጀግኖች በወያኔ ወህኒ ቤቶች እየማቀቁ፤ በየእለቱ ሰቆቃ (ቶርቸር) እየተፈፀመባቸው መሆናቸው በሀዘንና በቁጭት እናስባቸዋለን።
በሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የሴቶች ተሳትፎ አስፈላጊነት በመፈክር ደረጃ አንስተን የምንተወው ጉዳይ አይደለም። የሴቶች ተሳትፎ ያልታከለበት ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ግቡም አይመታም፤ ቢመታም ዋጋ የለውም።
ከጥቂት ዓመታት በፊት የተካሄዱትን የሰሜን አፍሪቃና የመካከለኛው ምሥራቅ አብዮቶችን በአንክሮ የተከታተለ ማንኛውም ሰው ከሚገረምባቸው ነገሮች አንዱ ሴቶች ያሳዩት ቆራጥነት እና ያካሄዱት ብስለት የተሞላው ትግል ነው። በቱኒዚያ የወጣቶች እንቅስቃሴ ውስጥ ወጣት ሴቶች ከመጀመሪያው ጀምሮ የአመራር ቦታ በመያዝ ተሳትፈዋል። በግብጽም የወጣት ሴቶች እልህ ከወንዶቹ በልጦ ታይቷል። አሁን በዩክሬን ውስጥ የምናየው ሀቅም ይህንኑ የሚያረጋግጥ ነው።
የሴቶች በሕዝባዊ አብዮቶች በስፋት መሳተፍ ከቁጥር ማብዛት እጅግ የላቀ መሠረታዊ ጠቀሜታዎች አሉት። ጥቂቶቹን እንደሚከተለው መዘርዘር ይቻላል።
  1. ለሴቶች ያልተመቸ ሥርዓት ለማንም አይመችም። ለማኅበረሰብ በጠቅላላ የሚመች ሥርዓት መገንባት ማለት በቅድሚያ ለሴቶች የሚመች ሥርዓት መገንባት ማለት ነው። ይህ ሥርዓት ደግሞ እነሱ እራሳቸው እየተሳተፉበት፤ ከዚያም አልፎ እየመሩትም ነው መገንባት ያለበት።
  2. ሴቶች ከወንዶች በላይ ታጋሾች ናቸው፤ ሲያመሩ ደግሞ በቀላሉ አይመለሱም ተብሎ ይታመናል። እናም የሴቶች በተቃውሞ ትግል ውስጥ በብዛት መሳተፍ ሥርዓቱ በሕዝቡ ምን ያህል እንደተጠላ ግልጽ አመላካች ነው።
  3. የወጣት ሴቶች በድፍረት ለተቃውሞ አደባባይ መውጣት ወጣት ወንዶችን ያጀግናል። የወጣት ወንዶች መጀገን ደግሞ ወጣት ሴቶቹን ይበልጥ ያጀግናል። ወጣት ሴትና ወንዶች በእርስ በርስ አርዓያነት ይጀጋገናሉ። እናም ወጣት ሴቶች አምረው ተነሱ ማለት ሁሉም ወጣቶች ሁሉ አምረው ተነሱ ወደማለት ያመራል።
  4. የእናቶች መቁረጥ አባቶችን ያነሳሳል፤ የእናትም የአባትም መነሳት ደግሞ መላው ቤተሰብ በሥርዓቱ ላይ እንዲነሳ ያደርገዋል። እናም እናቶች አመረሩ ማለት መላው ቤተሰብ አመረረ ማለት ይሆናል።
  5. የሴቶች በትግል አመራር ቦታ ላይ መገኘት በተቃዋሚዎች መካከል ኅብረትን፣ መተሳሰብን ባጠቃላይም ቤተሰባዊ ስሜት ይፈጥራል።
  6. ሴቶችና ወንዶች አብረው ሲቆሙ ነው የመተባበር ጥቅም በጉልህ የሚታየው!
የእህቶቻችን በድፍረት ድምፃችሁን ማሰማት ያለው ትርጉም ከድምፃችሁ ከፍታ እና ከቁጥራችሁ በላይ ነው። ዛሬ ጥቂት እንኳን ብትሆኑ ነገ ብዙዎቻችን አርዓያነታችሁን እንድንከተላችሁ ያደርገናል። እናም እህቶቻችን በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ባሳያችሁን ድፍረት ተበረታተናል። ኢትዮጵያ ብሩህ ራዕይ ያላት፤ ቆራጥነትን የተላበሱ ወጣቶች ያሏት መሆኑን አሳይታችናል። ይህ ትንሽ ጅምር የትልቅ ሕዝባዊ ማዕበል መንገድ አመላካች ነው።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ዘረኛውንንና አምባነኑን ወያኔ ከጫንቃችን ለማውረድ በምናደርገው ትግል የእህቶችና የእናቶች ተሳትፎ ወሳኝ እንደሆነ ያውቃል፤ ስለሆነም ሴቶች ትግሉን በስፋት እንዲቀላቀሉ ጥሪ ያደርጋል። ሴቶችና ወንዶች፤ ወጣቶችና አረጋዊያን ሁላችንም የወያኔን ዘረኛ አገዛዝን እንዲያበቃ በጽናት እንታገል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

onsdag 12. mars 2014

Ethiopia: Hackers Without Borders



March 11, 2014
Photograph: Raphael Satter/AP
by Joshua Kopstein
The New Yorker
Photograph: Raphael Satter/AP
Before Edward Snowden sparked a global debate about government surveillance, it was a fact of life for Tadesse Kersmo. During Ethiopia’s national elections, in 2005, he and his wife campaigned for the country’s pro-democracy party, the Coalition for Unity and Democracy, which achieved a sweeping victory in the capital of Addis Ababa. But, when the results were overturned and protests broke out amid allegations of fraud, the ruling party quickly began cracking down on the opposition. Observers from the European Unionreported extensive human-rights violations in the months that followed, including nearly two hundred demonstrators killed by security forces and tens of thousands more imprisoned.
Kersmo evaded arrest and moved to the countryside, but his ties to the opposition subjected him to continued threats, harassment, and intense monitoring long after the election. “It is common wisdom that the phones are tapped,” he told me, in a tired baritone, over Skype. “People would call me and tell me, ‘We are following you, we know what you’re doing, we know where you are.’ ” On three separate occasions between 2005 and 2007, Kersmo was detained and beaten. At one point, he was told that his family would find his dead body in the streets, because the prisons were filled to capacity. When that seemed imminent, in 2009, Kersmo and his wife fled to the U.K., where they were granted asylum. There he continued his work as a university lecturer and a senior member of Ginbot 7, an exiled pro-democracy party that the Ethiopian government labelled a terrorist group in 2011, under a vague and widely condemned proclamation.
Kersmo and his wife thought that their new life in the U.K. would take them out of the government’s sights. But, in April of last year, Kersmo read a report from the University of Toronto’s Citizen Lab, a nonprofit research group that scans the Internet to expose government-sponsored spyware and cyberattacks, showing evidence of a malware campaign targeting Ethiopian dissidents. The report describes a malicious file that, when opened, silently installs monitoring software on the victim’s computer. When Kersmo noticed that the malware “baited” its victims using photos of Ginbot 7 members, including those of himself, he decided to have his machine examined by Citizen Lab.
The group found traces of FinSpy, part of an “intrusion” software suite known as FinFisher, which first made headlines in 2011, after a sales contract was discovered inside the headquarters of the Egyptian secret police, following the ouster of President Hosni Mubarak. The spyware was capable of stealthily transmitting Kersmo’s chats, Web searches, files, e-mails, and Skype calls to a server somewhere in Ethiopia. “The feeling was shock—that they are still following us, even here,” Kersmo told me. “It goes beyond my personal security. All Ethiopians living in the U.K., United States, and elsewhere are unsafe now.”
The other week, Privacy International, a U.K.-based human-rights organization, filed a criminal complaint on Kersmo’s behalf, making him the first U.K. resident to challenge the use of hacking tools by a foreign power. “This case would be important to all refugees who end up in countries where they think they are safe,” Alinda Vermeer, a lawyer with Privacy International, who filed Kersmo’s complaint, told me in a phone interview. That sense of safety is illusory, she said, because countries armed with tools like FinSpy insure that refugees “can be spied on in an equally intrusive way as they were back at home.” Worse, the surveillance also reveals with whom the victims have been communicating, potentially endangering the lives of contacts and relatives still residing in their home country.
Kersmo’s dilemma is becoming more common, particularly among journalists and activists seeking political freedoms beyond their country’s borders. The Electronic Frontier Foundation recently filed a suit similar to Kersmo’s against the Ethiopian government, on behalf of a U.S. citizen living near Washington, D.C., where most of the country’s Ethiopian-American population lives. (Fearing government reprisal, the plaintiff asked to use a common Ethiopian name, “Kidane,” as a pseudonym during the proceedings.) In a different report, released last month, Citizen Lab revealed evidence of an attack on Ethiopian Satellite Television, a news service with offices in the U.S. that serves as an alternative to state-controlled media in Ethiopia. A mysterious source had made three attempts to send malicious files to employees, claiming that they were news articles; the files contained a small program that exploits a security flaw in Microsoft’s Windows operating system, allowing it to silently install Remote Control System, a spyware tool similar to FinSpy.
The growing surveillance-technology industry—including the companies Gamma International and Hacking Team, the European developers of FinSpy and Remote Control System—has been valued at five billion dollars. Proponents defend such commercial spyware by noting that it helps authorities catch terrorists and other serious criminals. But Gamma will not disclose which countries it sells its products to, nor is it particularly eager to take responsibility for how they are used. In 2012, Martin J. Muench, the company’s founder, told Bloomberg News that his company has “no control; once it’s out there it’s basically with the country” to use the tools ethically. (Gamma did not respond to a request for comment.)
The Milan-based Hacking Team claims that it monitors its software, and has the ability to disable functionality if it believes that clients “have used Hacking Team technology to facilitate gross human rights abuses.” According to its customer policy, the company’s sales are reviewed by “an outside panel of technical experts and legal advisors,” which looks for “red flags,” including “credible government or non-government reports reflecting that a potential customer could use surveillance technologies to facilitate human rights abuses.” Like Gamma, Hacking Team also refuses to name which countries use its products, but itdenied allegations in a recent report by Citizen Lab that claimed Remote Control System was used in twenty-one countries, including Azerbaijan, Uzbekistan, Saudi Arabia, and Sudan. A spokesperson, Eric Rabe, told Mashable that the Citizen Lab report is “not an accurate list of nations where Hacking Team clients are located,” but refused to elaborate on the company’s vetting process.
Regardless, the increased scrutiny of commercial spyware has led some countries to tighten regulations regarding its sale, particularly across national borders. In 2012, the U.K. government informed Gamma, which has offices in Andover, England, that it needs to obtain licenses to sell FinSpy outside the country, citing laws that control the export of cryptography. Alinda Vermeer, of Privacy International, explained that, while export controls under the Wassenaar Arrangement—which regulates weapons and technologies with potential military applications within forty-one nations—were recently updated to restrict spyware, the new terms haven’t yet been adopted by all participating countries. This means that, while future deals will be regulated in some countries, past purchases and current efforts from spyware companies around the world have relatively few rules to follow—and more people like Kersmo are bound to get caught in the crosshairs. “There is a social obligation for corporations,” Kersmo said. “Selling this kind of software to irresponsible governments is irresponsible.”
Joshua Kopstein is a cyberculture journalist from New York City.


onsdag 5. mars 2014

“ነገረ ኢትዮጵያ” የሰማያዊ ፓርቲ ጋዜጣ ወቅታዊ ጉዳዮችን ይዛ ወጥታለች


  • ውህደት ወይስ ትብብር?
  • ስለ ሀገርና ወገን የሚታገሉትን ማዋከቡ ይቁም! (ርዕሰ አንቀጽ)
  • “አገርን ከመቁረስ በላይ ምንም ነገር ሊመጣብን አይችልም”
  • “መንግስት›› አሳልፎ የሰጠው ሉዓላዊነት”
                               [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]
Semayawi Party newspaper "Negere Ethiopia" Issue 2

søndag 2. mars 2014

ጥፋተኛ ጥፋቱን በይቅርታ እንጂ በዉሸትና በዕብሪት መሸፈን አይችልም

በቅርቡ አንድም የወያኔ ጌቶቹን ለማስደሰት ደግሞም ከህወሃት ካድሬዎች ስድብና ግልምጫ የማያድን ጎደሎ ስልጣን ለማግኘት ሲል ተወልዶ ያደገበትንና እመራዋለሁ የሚለዉን የአማራን ህዝብ ክብርና ታሪክ ያጎደፈዉና ያዋረደዉ የአለምነዉ መኮንን አስጸያፊ ንግግር በአለም ዙሪያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያንን ያስቆጣና ያነሳሳ ጉዳይ ሆኖ መሰንበቱ ይታወሳል። ይህ የአማራን ህዝብ ማንነትና ይህ ጀግና ህዝብ በኢትዮጵያ ታሪክ ዉስጥ ያለዉን አኩሪ ቦታ ያላገናዘበና ባልተሞረደ አንደበት የተነገረ አስጸያፊ ንግግር ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተዉን የአማራን ህዝብ ብቻ ሳይሆን አገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ የሚኖሩትን በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን አስቆጥቷል። አይናቸዉ ከገንዘብና ከሥልጣን ዉጭ ሌላ ምንም ነገር የማይመለከት ለሆዳቸዉ ብቻ ያደሩ ሰዎች የተከፈተ ሆዳቸዉንና ማለቂያ የሌለዉ የሥልጣን ጥማታቸዉን ለማርካት ሲሉ ምንም ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይሉ ወያኔ በሥልጣን ላይ የቆየባቸዉ ያለፉት ሃያ ሦስት አመታት በግልጽ አሳይተዉናል። ሆኖም ግን አይናቸዉ የታወረና ጭንቅላታቸዉ ባዶ የሆነ ሰዎች በነገሱበት በወያኔ ስርዐት ዉስጥም ቢሆን የሚጠሉትን፤ የሚንቁትንና የገዛ ወገኖቹን የገቡበት ቦታ ሁሉ እየተከተሉ ወደ አገራችሁ ግቡ እያሉ የሚያፈናቅሉ ዘረኞችን ለማስደስት ሲል ስቃይ የበዛበትን የራሱን ህዝብ ያዋረደ ከሀዲና ሂሊና ቢስ ሰዉ ያየነዉ አንድ አለምነዉ መኮንንን ብቻ ነዉ። አለምነዉ የተናገራቸዉን አጥንት የሚሰብሩ የንቀት ቃላት ይሀንን ከንቱ ሰዉ ባወገዝን ቁጥር እየደጋገምን ብንጠቅስ በአንድ በኩል የወያኔን ዘረኞች አላማ ያራምዳል ብለን ስለምናምን በሌላ በኩል ደግሞ እንደዚህ አይነቱን ጸያፍ ንግግር መደጋገም ሂሊናችን ስለማይፈቅድንና የጠፈፈ ቁስል መቆስቆስ ይሆናል ብለን ስለምንሰጋም ንግግሩን አንደግመዉም።
አሜሪካንን በመሳሰሉና በዕድገት ወደፊት በገፉ አገሮች ዉስጥ ዉሻ የሚታወቀዉ የሰዉ ልጅ ታማኝ ወዳጅ በመባል ነዉ። ዉሻ ባለቤቱን ለማስደስት ጭራዉን ከመቁላት ባሻገር የባለቤቱን እግር ይልሳል፤ ይንበረከካል፤ እግር ስር ይተኛል፤ ደግሞም አምጣ ብለዉ የወረወሩለትን ነገር እየሮጠ ሄዶ ያመጣል። የሚገርመዉ እንስሳዉ ዉሻ እንኳን እነዚህን ነገሮች ሁሉ የሚያደርገዉ ለባለቤቱና ለለመደዉ ወዳጁ እንጂ ለሌላ ለማንም ሰዉ አያደርግም። ዉሻ ባለቤቱንና ወዳጁን በተለይ ደግሞ የሱንና የባለቤቱን ጠላቶች ለይቶ ያዉቃል፤ ስለዚህም ዉሻን ባለቤትህን ንከስ ብለን ያንን የሚወደዉን ስጋ ያሻንን ያክል ብናሸክመዉ እኛዉ ላይ መልሶ ይጮህብን እንደሆነ ነዉ እንጁ ዉሻ ባለቤቱን በፍጹም አይነክሰም።
ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ እነ አለምነዉን የመሳሰሉ ለወያኔ ያደሩ ሂሊና ቢሶች፤ ሹምባሾች፤ ምስለኔዎችና ሆዳሞች አንድ የጎደላቸዉ ትልቅ ነገር ቢኖር የዉሻን ያክል ታማኝ መሆን ነዉ። እነ አለምነዉ እናስተዳድረዋልን ለሚሉት ህዝብ ታማኝነት ቢኖራቸዉ ኖሮ ዛሬ እነሱ እራሳቸዉ፤ የሚመሩት የአማራ ህዝብም ሆነ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ከአገሩ ተስድዶ እንደ አዙሪት በየአገሩ ከሚዞር በገዛ አገሩ ተከብሮ በወግና በማዕረግ ይኖር ነበር።ችግሩ “ባለቤቱ ያቀለለዉን አሞሌ ባለዕዳ አይቀበለዉም” ነዉና የኢትዮጵያ ህዝብ በእነ አለምነዉና መሰሎቹ የተነሳ ኢትዮጵያ ዉስጥም ከኢትዮጵያ ዉጭም መብቱንና ነጻነቱን ተገፍፎ የሚኖር ባተሌ ህዝብ ሆኗል። የአማራ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት ነኝ ባዩ አለምነዉ መኮንን እንደማናችንም እግዚአብሄር በአምሳያዉ የፈጠረዉ ሰዉ ነዉ፤ ታድያ ለምንድነዉ ሂሊና የሌላቸዉና ነገሮችን አመዛዝነዉ የመመልከት ባህሪይ የልታደላቸዉ እንስሳት እንኳን የማያደርጉትን አስጸያፊ ነገር እሱ በገዘ ወገኖቹ ላይ ያደረገዉ? በእርግጥ ይህንን ጥያቄ አለምነዉ በጥቅም የተገዛ ወይም ለሆዱ ያደረ ሰዉ ነዉ ብለን በቀላሉ መልሰን ማለፍ እንችል ይሆናል፤ ነገር ግን የኢትዮጵያ ህዝብ ከብዙ አፍሪካዉያን በተለየ መልኩ ነጻነቱንና አንድነቱን ጠብቆ መኖር የቻለበትን ምክንያት ለምንረዳ ሰዎች ለዚህ ጥያቄ የሚሰጠዉ መልስ የችግሩን ያክል የተወሳሰበ መሆኑን እንረዳለን። ይህንን ስለምንረዳም ነዉ ኢትዮጵያንና ህዝቧን ከወያኔ መዳፍ ዉስጥ ፈልቅቆ ለማዉጣት መከፈል ያለበት መስዋዕትነት የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ቤት ያንኳኳል የምንለዉ።
ወያኔ ወይም ህወሀት በሚባለዉ የዘረኞች ድርጅት ዉስጥ የታቀፉ ሰዎች ስልታዊ አላማ አንድና አንድ ብቻ ነዉ- እሱም ኢትዮጵያ የምትባል ገንዘብና ንብረት የምትታለብ ላም ወተቷ እስኪነጥፍ ድረስ ብቻችንን እንለባት የሚል የስስት አላማ ነዉ። ይህንን የስስት አላማ ተግባራዊ ለማድረግ የነደፉት እስትራቴጂ ደግሞ የአላማችን ዋነኛ ጠላት ነዉ ብለዉ የሚያምኑትን የአማራዉን ህዝብ መግደል፤ ማሰር፤ ማሳደድ፤ ማፋናቀል፤ መደብደብና ማዋረድ ነዉ። ይህንን ከጠላቶቻችን ከነሙሶሊኒና ግራዚያኒ የተማሩትን አማራዉን የማሳነስና የማጥፋት ስልት ደግሞ እግራቸዉ አዲስ አበባን ከረገጠበት ቀን ጀምሮ የአማራዉን ግዛት ቆርሰዉ የራሳቸዉ በማድረግና አማራዉን በመግደል፤ በማሳደድና በማሰር በተግበር አሳይተዉናል ዛሬም እያሳዩን ነዉ።
የወያኔ ዘረኞች የቂም በቀል እርምጃዎች ሁሉ ያነጣጠሩት በአለምነዉ መኮንንና በወገኑ የአማራ ህዝብ ላይ ነዉ፤ ወያኔ ወልቃይት ጠገዴን ቆርሶ የወሰደዉ ከአለምነዉ መኮንንና ከወገኑ ከአማራ ህዝብ ላይ ነዉ፤ ከጉራ ፈርዳና ከቤንሻንጉል አካባቢዎች ሂድ ከዚህ ተብሎ የተፈናቀለዉ ህዝብ አለምነዉ መኮንን እመራዋለሁ የሚለዉ የአማራዉ ህዝብ ነዉ። ታድያ አለምነዉ መኮንን እሱንና የገዛ ወገኖቹን ለዘህ ሁሉ ዉርደትና መከራ የዳረጉትን የወያኔ ዘረኞች ለማስደስት ሲል የተወለደበትን ማህበረሰብ መሳደቡ ምን ይባላል? ወያኔ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያስተማረዉ መጥፎ ነገር ቢኖር ዘረኝነት ነዉ፤ አለምነዉ መኮንን በዚህ መጥፎ የወያኔ ትምህርት ተለከፈ ብለን ብናምን እንኳን ዘረኝነት የራስን ዘር ከሁሉም በላይ እንድናይና ሌሎችን እንድንጠላና እንድንንቅ ያደርገናል እንጂ የራሳችንን ዘር እንድንሰድብና እንድናዋርድ አያደርገንም። ታድያ አለምነዉ መኮንንን የተጠናወተዉ የወያኔ ዘረኝነት ነዉ ወይስ የሚያድኑትን እያስጠላ የሚገድሉትን የሚያስወደድ የታምራት ላይኔ በሽታ ነዉ?
ሌላዉ የአለምነዉ መኮንንና የብአዴን ችግር አለምነዉ ያንን አሳፋሪ ንግግር ካደረገና ንግግሩ የህዝብ ጆሮ ዉስጥ ገብቶ አገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ ብዙ ሰዎችን ካስቆጣ በኋላ ጥፋታቸዉን ተረድተዉ ህዝብን ይቅርታ አለመጠያቃቸዉና ሌላ ቢቀር አስተዳድረዋለሁ የሚለዉን ህዝብ ሙልጭ አድርጎ የሰደበዉን ሰዉ ህዝብን ከመምራት ሀላፊነት ቦታ ላይ እንዲነሳ አለማድረጋቸዉ ነዉ። አለምነዉ መኮንን የአማራን ህዝብ ከተሳደበ በኋላ ወያኔም ሆነ ብአዴን ከመጋረጃ ጀርባ የተባባሉትን ነገር ባናዉቅም ስድቡን አስመልክቶ በግልጽ ህዝብ እንዲያዉቀዉ የወሰዱት ምንም እርምጃ እንደሌለ ግን በሚገባ እናዉቃለን። ይህ የሚያሳየን ወያኔና ብአዴን ለህዝብና ለአገር ምንም ደንታ እንደሌላቸዉ ብቻ ሳይሆን እነዚህ ሁለት ጸረ ህዝብ ድርጅቶች ህዝብን እንዳሻን ረግጥን መግዛት እንችላለን የሚሉ ዕብሪተኞች እንደሆኑ ነዉ። የወያኔ ሹሞችና በየቦታዉ የበተኗቸዉ ሆዳም አፈቀላጤዎቻቸዉ የአለምነዉ መኮንንን መረን የለቀቀ ንግግር ለማስተባበልና እንዲያዉም ተባለ የተባለዉ ንግግር ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሆን ብለዉ ያቀነባበሩት የፈጠራ ስራ ነዉ እያሉ ህዝብን ለማሳመን ብዙ ደክመዉ ነበር፤ ነገርግን ብዙም ሳይቆይ ግለሰቡ በባዕዴን ስብሰባ ላይ የደረገዉ ንግግር በመጀመሪያ በኢሳት ሬድዮና ቴሌቪዥን ከዚያም በማህበራዊ ሜድያዎችና በተለያዩ ድረገጾች ላይ በብዛት መሰራጨት ሲጀምር ወያኔና ቡችሎቹ ማስተባበሉን ትተዉ ሳይወዱ በግድ ዝምታን መርጠዋል።
ወያኔና ብአዴን ህዝብን ሰድበዉና አዋርደዉ ዝምታን ቢመርጡም የተሰደበዉ የኢትዮጵያ ህዝብና መሪ የፖለቲካ ድርጅቶቹ ግን የአማራን ህዝብ አስጸያፊ ስድብ የሰደበዉ አለምነዉ መኮንን ከጥፋቱ ጋር ተመጣጣኝ የሆነ እርምጃ እስካልተወሰደበት ድረስ ዝም እንደማይሉ ለሚመሩት ህዝብም ለወያኔም ይፋ አደረጉ። በተለይ አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲና መላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ አለምነዉ መኮንን የሰደበዉ የአማራ ህዝብ በክልሉ ዋና ከተማ ባህር ዳር ዉስጥ በነቂስ ወጥቶ ተቃዉሞዉን እንዲያሰማ የሰላማዊ ሠልፍ ጥሪ አደረጉ። ይህ የተቃዋሚ ፓርቲዎች የሠላማዊ ሠልፍ ጥሪ ለህዝብ ከተላለፈና ህዝቡ ቁጣዉን ከመግለጽ ወደኋላ እንደማይል ከተረዱ በኋላ ነበር እነ አለምነዉ መኮንን ሰድብዉት እንዳሻህ ብለዉ የዘጉትን ህዘብ በፕሬስ መግለጫ ስም እንደገና ማደናገር የጀመሩት። እዚህ ላይ አንድ እጅግ በጣም የሚያናድድና አንጀት የሚያሳርር ነገር ቢኖር ባለፈዉ ሐሙስ አለምነዉ መኮንን በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በጉጉት ይጠበቅ የነበረዉ ይህ ግለሰብ የሰደበዉን ህዝብ ይቅርታ ይጠይቃል ተብሎ ነበር። ሆኖም አለምነዉ መኮንን፤ብአዴንና ህወሀት ከዕባብ እንቁላል አርግብ እንደማይጠበቅ በግልጽ አሳይተዉናል።
ባለፈዉ ኃሙስ ዬካቲት 13 ቀን 2006 ዓም አለምነዉ መኮንን የአገር ዉስጥ ጋዜጠኞች ያንን መረን የለቀቀ ስድቡን አስመልክተዉ የጠየቁትን ጥያቄ ሲመልስ እዉነትም “ከባዶ ጭንቅላት ባዶ እግር ይሻላል” የሚያሰኝ የቂል መልስ ስጥቷል። ነፃ ሜድያ በሌለባት ኢትዮጵያ ዉስጥ እንዳሰኘዉ መለፍለፍ የለመደዉ አለምነዉ መኮንን “ተቃዋሚዎች አለ ያሉትን ነገር እኔ በፍጹም አላልኩም . . . እኔ ለህዝብ ክብር ያለኝ ሰዉ ነኝ በማለት ነገሩ እየቆየ ሲሄድ እሱ እራሱ የተናገረዉ ንግግር ገርሞት “እኔ እንዴት እንደዚህ ልል እችላለሁ”ሲል ጋዜጠኞች የጠየቁትን ጥያቄ መልሶ እራሱን ጠይቋል። ይህ እፍረተ ቢስ ሰዉ ህዝብን የተሳደበዉ አልበቃ ብሎት ጭራሽ ጥፋቱን በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ ለማላከክ ሲሞክር ተድምጧል። ማንም ሰዉ ተናገር ብሎ ሳያስገድደዉና ቁጭ ብለዉ የሚያዳምጡት ሰዎች እየሳቁ በራሱ አንደበት የተናገረዉን ፀያፍ ንግግር ተቃዋሚዎች መሪዎችን ከህዝብ ለመነጠል ሆን ብለዉ የሰሩትና በቆርጦ ቀጥል የኮምፒተር ዘዴ ያቀነባበሩት ነገር ነዉ እንጂ ዬኔ ንግግር አይደለም ሲል የራሱን ድምፅ ዬኔ አይደለም ሲል ሽምጥጥ አድርጎ ክዷል።
ከአህያ ጋር የዋለች ጊደር ተምራ የምትመጣዉን ነገር እናዉቃለንና ከወያኔ ዘረኞች ጋር ለአመታት የከረመዉ አለምነዉ መኮንን በመዋሸቱ ብዙም ላንፈርድበት እንችላለን፤ ደግሞም ወያኔና ዉሸት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸዉና ወያኔን ባየን ቁጥር ትዝ የሚለን እንደ ሰዉ ቆሞ የሚሄደዉ ዉሸቱ ነዉና የአለምነዉ ዉሸት በፍጹም አይገርመንም። ይልቅ እኛን የገረመን አለምነዉ መኮንን የራሱን ድምጽ ዬኔ አይደለም ማለቱ ነዉ። መቼም አንድ ሰዉ ለይቶለት አማኑኤል ካልገባ በቀር እኔ “እኔ” አይደለሁም ብሎ የመናገር ደረጃ ላይ የሚደርስ አይመስለንም። ደግሞስ አለምነዉ መኮንን የማንሰማዉ መስሎት ባልተገራ አንደበቱ ህዝብን ሲሳደብ በድንገት ሰምተነዉ ነዉ እንጂ እስኪ እግዚአብሄር ያሳያችሁ አለምነዉ መኮንንን ማን ከቁም ነገር ቆጥሮት ነዉ የሱን ተራ ንግግር አየቆረጠ የሚቀጥለዉ? ማንስ ስራ የፈታ ሰዉ ነዉ የራሱንና የኮምፒተሩን ግዜ የአለምነዉ መኮንንን ቆሻሻ ንግግር ቆርጦ በመቀጠል የሚያጠፋ?
ሌላዉ የአለምነዉ መኮንን ጉድ ይህ ሴራ ተቃዋሚ ድርጅቶች መሪዎችን ከህዝብ ለመነጠል የሚያደርጉት ሴራ ነዉ ብሎ መናገሩ ነዉ። ወይ ጉድ . . . “ ወግ ነዉ ሲዳሩ ማልቀስ” ይላል የአገራችን ሰዉ። ለመሆኑ ጭንቅላተ ባዶዎቹ የወያኔና የብአዴን መሪዎች ቀድሞዉኑ ከህዝብ ጋር መች ገጥመዉ ያዉቃሉና ነዉ ተቃዋሚ ድርጅቶች እነሱንና ህዝብን ለመነጣጠል እያሴሩ ነዉ ተብሎ የሚነገረዉ? ወንድምዬ የምትሰማኝ ከሆነ እናንተና ህዝብ ዉኃና ዘይት ናችሁ፤ ተገናኝታችሁም አንድ ላይ ሆናችሁም አታዉቁም። በዚህ ስድባችሁ፤ ክህደታችሁና ዕብሪታችሁ ደግሞ ለወደፊትም ቢሆን ከህዝብ ጋር አትገጥሙም። ከህዝብ የነጠላችሁ ክፉ ስራችሁና መጥፎ ጠባያችሁ ነዉ እንጂ ተቃዋሚዎች አይደሉም።
አለምነዉ መኮንን እሱ እራሱ የአማራ ተወላጅ ነዉ፤ ያንን የመሰለ አስጸያፊ ንግግር የተናገረዉም በአማራ ህዝብ ላይ ነዉ፤ሆኖም በዘለፋዉና በዉርደቱ አንጀቱ ያረረዉ ወይም ዘለፋዉ ያነጣጠረዉ በአማራ ህዝብ ላይ ብቻ ነዉ ብለን የምናስብ ሰዎች ካለን እኛም ዘለፋዉን እንደሰነዘረዉ ሰዉ እራሳችንን ስተናል፤ ወይም ዋነኛዉ የወያኔ ወጥመድ ዉስጥ ገብተናል አለዚያም አርቆ የመመልከት ችሎታችን ከከዳን ቆይቷል ማለት ነዉ። ዘለፋዉና ንቀቱ የተሰነዘረዉ በሁላችን ላይ፤ ነዉ፤ የተዋረድነዉም ሁላችንም ነን፤ ስለሆነም አለምነዉንና አቅፈዉት ከለላ የሰጡትን ሁሉ ለፍርድ ለማቅረብ የሚደረገዉ ትግል የሁላችንም ትግል መሆን አለበት። ባህር ዳር ዉስጥ የታየዉ ህዝባዊ ቁጣ በመላዉ ኢትዮጵያ እንደ ሰደድ እሳት ተቀጣጥሎ ወያኔ የገነባዉን ዘረኛ ስርዐት ለብልቦ ከምድረ ኢትዮጵያ እስኪያጠፋ ድረስ ትግላችን መቀጠል አለበት። በዚህ ትግል ዉስጥ “እኔ” ወይም “አንተ” የሚባል ቃል በፍጹም ሊኖር አይገባም። የትግላችን ብቸኛ መነሻና መድረሻ “እኛ “ ብቻ መሆን አለበት። ወያኔን አጥፍተን እንደ ህዝብና እንደ አገር በሠላም፤ በነፃነትና በብልጽግና መኖር የምንችለዉ ኢትዮጵያዊነታችን “እኛ” በሚለዉ አስተሳሰብ ላይ ሲገነባ ብቻ ነዉ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

የዩናይትድ እስቴስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኢትዮያ ዉስጥ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳለ በዘንድሮዉ አመታዊ ሪፖርቱ ይፋ አደረገ



ዋሽንግተን ዲሲ፤ የካቲት 20/2006 (ቢቢኤን) ፦ የዩናይትድ እስቴስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት (State Department) ባወጣዉ የዘንድሮ የሰዓዊ መብት ሪፖርት ላይ የኢትዮጵያ መንግስት ያከናዉናቸዋል ያለዉን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በመዘርዘር ሰፋ ባለ መልኩ አቅርቦታል።
ቀድም ሲል ኢትዮጵያ ዉስጥ በ2003 በተደረገዉ ምርጫ፤ በሟቹና በቀድሞው ጠቅላይ ሚንስቴር መለስ ዜናዊ ይመራ የነበርዉ ኢ.ህ.አዴ.ግ ከ547 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ 545 መቀመጫዎች አሸንፏል መባሉን ሪፖርቱ እያመላከተ የምርጫ ጣቢያዎች በመንግስት ሐይላት ቁጥጥር ስር እንደነበሩና አለምአቀፍ ታዛቢዎች ስራቸዉን በተገቢዉ መልኩ እንዳያከናዉኑ ገደብ እንደነበረባቸዉ ይገፃል።
John Forbes Kerry current United States Secretary of State.
በአገሪቱ ዉስጥ ባለዉ ከፍተኛ የመብት ረገጣ ሳቢያ ዜጎች የመሰብሰብ፣የመደራጀት፣የመናገር መብትን በገሃድ እንደሚነፈጉ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ያስደረግቸዉን ጥናቶች ተመርኩዞ ያብራራል። እነዚህን የዲሞክራሲ እሴቶችን ለመተግበር የሚሞክሩም ይታሰራሉ፣ይንገላታሉ፣ይዋከባሉ፣ዛቻ ይደርስባቸዋል፣ ክብራቸዉ ተነክቶ እንዲሸማቀቁምይደረጋሉ በማለት ሪፖርቱ ያትታል።እርዳታን የሚያስተባብሩ፣ እርዳታን ለጋሽ የሆኑ ድርጅቶች፣ ማህበራዊና ትርፍ አልባ የሆኑ ተቋማት (NGO) የግብረ-ሰናይ ተልእኮ አቸዉን እንዳይፈጽሙ የኢትዮጵያ መንግስት እንደሚከለክል፤ በሰዎች ላይ ህገ ወጥ የሆነ ግድያ እንደሚፈጽም፣ዜጎች ግርፋት-ድብደባ እንደሚደርስባቸዉ፣ ወጥ የሆኑ የማሰቃያ ተግባራት በመንግስት ሐይላት እንደሚፈጽምና በአገሪቱ እስርቤት የሚገኙ ታሳሪዎችን ህይወት ለአደጋ የሚያጋልጹ አሳቃቂ ተግባራትም እንዳሉም በሪፖርቱ ላይ ተገልጿል።
ሰዎች በፍርድ ቤት ሳይበየንባቸዉ በጅምላ ተይዘድዉ ይታሰራሉ፤በፍርድ ቤት የአሰራር ዘይቤም ይሁን በፍትህ ሒደቱ ዉስጥ ግልጽ የሆነ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት አለበት፤ ፍርድ ቤቶችም ደካማ ናቸዉ! ሲል ሪፖርቱ ይደመድማል። መንግስት ሀሳብን በነጻነት ለመግለጽ የሚሞክሩ ያገሪቱ ዜጎች ላይ ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እንደሚወስድ በዝርዝር የተቀመጠ ሲሆን፤ በነሐሴ 2/2005 የኢድ-አልፈጥር በዓል በሚከበርበት ወቅት፤ በሰላማዊ መንገድ ተቃዉሞ ያሰሙ ከነበሩት ሙስሊም ኢትዮጵያዉያን መካከል ከ 1000 በላይ የሚሆኑት በጅምላ ተግበስብሰዉ መታሰራቸዉና ከመካከላቸዉም የሞቱ መኖራቸዉ በሪፖርቱ ላይ አጽንኦት ተሰጥቶታል።የዜጎች ግላዊ መብትን በመግፈፍ፤ በሙስሊሙ ማህበረስብ ላይ ህገወጥ የሌሊት ፍተሻዎችም ተደርገዋል። ግልጽና ስልታዊ በሆነ መልኩም ከቦታ ወደ ቦታ ዜጎችን የማፈናቀል መርሃግብር በመንግስት መፈጸሙን የሚያስረዳዉ ሪፖርት ነጻ መሆን የሚገባዉ የመማርና የማስተማር ሒደት የመንግስት ጣልቃገብነት እንዳለበትም ይገልጻል።
ዜጎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸዉን ተጠቅመዉ በነጻነት መንግስትን የመቀየር አቅማቸዉ ሆን ተብሎ የተገደበ ነዉ!በፖሊስ፣በፍርድ ቤቶችና በመንግስት አመራር ዉስጥ በስልጣን መባለግ-ሙሰኝነት-ጉቦኝነት በገሃድ ይተገበራሉ። መንግስት በስልጣን የባለጉንና የህዝብን አደራ ያጎሳቆሉ ወንጀለኞች ችላ በማለት ፖለቲካዊ ዉለታን ይዉላል፤ ፖለቲካዊ ምህረትን ለምግባረ ብልሹ የመንግስት አካላት እንደሚያደርግ የዩናይትድ እስቴትስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሪፖርት ያጋልጻል።
በኢትዮጵያ ህገ መንግስት የጾታ እኩልነት የተረጋገጠ ቢሆንም በመንግስታዊ የአሰራር መዋቅር ዉስጥ ሴቶች ይጨቆናሉ። ህገወጥ የሆነ የሰዉ ዝዉዉር ይፈሰማል፣ የአካል ጉዳተኞች (የተሳናቸዉ) ማህበራዊ ጭቆና ይደርስባቸዋል፣የ ኤች.አይ.ቪ ኤድስ ህሙማን ማህበራዊ የሆነን በደል ይጋፈጣሉ፣የሰራተኖች መብት የተገደበ በመሆኑ ህፃናትን አስገድዶ የጉልበት ስራ ማሰራቱ የተለመደ መሆኑ በሪፖርቱ ላይ ተዘርዝሯል።
የመንግስት ሐይላት የሰዎችን ደብዛ ያጠፋሉ፤ የሰዎች መሰወር ይስተዋላል! በትግራይ ክልል በአላማጣ ከተማ መንግስት በልማት ስም ቤቶችን በሚያፈርስበት ወቅት አለመግባባት ተፈጥሮ የታሰሩ 12 የአካባዊ ተወላጆች የገቡበት እንደማይተዋቅ እና ተመሳሳይ በሆነ መልኩ በሶማሌ ክልል ያለዉ ልዩ የፖሊስ ሐይል በክልሉ ተወላጆች ላይ ኢሰብዓዊ የሆነ ማንገላታት፣ማሰቃየት፤ ግድያ እደሚፈጽም መታወቁ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ህገመንግስት ቶርቸር (ግርፋት ድብደባ ማሰቃየት)ይከለክላል። ቶርቸርን የመሰሉ የሰዉ ልጅን ክብር ገፋፊ የሆኑ ጭካኔ የተሞላባቸዉ ተግባራት፤በመንግስት የደህነነትና የጥበቃ ሐይላት እንደሚፈጸሙ በማጋለፅ በጥር 9/2005 የተያዘዉ የሙስሊሞች ጉዳይ መጽሔት አምድኛ እና ማኔጂንግ ኢዲተር የነበረዉ ጋዜጠኛ ሰለሞን ከበደ በማእከላዊ የምርመራ ማእከል ዉስጥ በተደጋጋሚ የዚሁ ህገወጥና አስከፊ ተግባር ሰለባ እንደነበር በዩናይትድ እስቴት የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሪፖርት ላይ በዋቢነት ተጠቅሷል።
በጥቅምት 8/2006 ሁማን ራይትስ ዎች ያወጣዉን ሪፖርት እንደ አብነት በመጥቀስ በመጥቀስ በማእከላዊ የምርመራ ማእከል ዉስጥ መርማሪዎች ታሳሪዎችን በማስገደድ የእምነት ቃል እንደሰጡ እንደሚያደርጉ የዩናይትድ እስቴትስ የዉጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት እየገለጸ፤ በማእከላዊ እስር ቤት ዉስጥ ከፍተኛ የሆነ ቶርቸር (ግርፋት-ድብደባ-ማሰቃየትት)፣ ዛቻ፣ማስፈራራርት፣ እስረኞች ላይ ዉሃ መድፋት፣የእስረኞችን እጅ ጣራ ላይ አስሮ ለረጅም ሰዓታት ማቆም፣እሰረኞችን ነጥሎ ለብቻ ማሰርን የመሳሰሉ ኢሰብዓዊ ተግባራት እንደሚፈጽሙና ዲፕሎማቶች፣ኤንጂኦ (በጎ አድራጊ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ትርፍ አልባ ድርጅቶች) እስረኞችን የመጎብኘት ፍቃድ እንደሚነፈጉ ተገልጿል።
በመስከረም 2005 በተገኘዉ መረጃ መሰረት ከ70,000 እስከ 80,000የሚድርሱ እስረኞች መኖራቸዉ ሲታወቅ፤ ከነዚህም መካከል 2500ሴቶች ሲሆኑ 600 ህጻናት ከእናቶቻቸዉ ጋር መታሰራቸዉ እና ታዳጊ ወጣቶች ከአዋቂዎች ጋር አብረዉ እንደሚታሰሩ ተዘግቧል። የአገሪቱ እስር ቤቶች በጣም የተጣበቡ ከመሆናቸዉም ባሻገር ወታደራዊ ተቋማትም እንደ እስር ቤት ማገልገላቸዉ ተዘግቧል። በርካታ እስረኞች ከመጣበብ፣ተነጥሎ ከመታሰር፣ የተማሏ የጤና ግልጋሎት ካለመኖሩ የተነሳ ለአእምሮ ህመም ይዳረጋሉ። ለአንድ እስረኛ የምግብ፣ የዉሃ አቅርቦትን ለመለገስ እና የጤና ግልጋሎት ለመስጠት በቀን ስምንት ብር ከአስር ሳንቲም ብቻ እንደተመደበ የዩናይትድ እስቴትስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አመታዊ የሰዓዊ መብት ሪፖርት ይዘረዝራል።
ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች ከ2004 ጀምሮ ሰላማዊ የሆነ ተቃዉሞን በአወሊያ የትምርት ተቋም ዉስጥ በመጀመር ከአርብ ስግደት (ከጁመዓ ሶላት) በሗላ በቀጣይነት የተቃዉሞ መርሃግብር እንደሚያከናዉኑና፤ ይህ የቅዋሜ ተግባር ምንም ሰላማዊ ቢሆንም የፖሊስ አካላት ሰዎችን በመያዝ አላስፈላጊ ሐይል እንደሚጠቀሙ ሪፖርቱ ያስረዳል። በሐምሌ 14/ 2004 በሙስሊሞች የተደረገዉን ሰላማዊ ተቃዉሞ ተከትሎ መንግስት “የደህንነት ሰጋት” የሚል ማመካኛን በመፍጠር 28 ሙስሊሞችን አስሮ በጥር 24/2005 ክስ ያቀረበባቸዉ ቢሆንም በታህሳስ 3/2006 አስሩን በነጻ አሰናብቶ በአስራ ስምንቱ ላይ ያቀረበዉን ክስ ዝቅ አድርጓል። መንግስት እነዚህን የሙስሊም ታሳሪዎች በአለማችን ላይ ከሚታወቁ አሽባሪ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት አላቸዉ ብሎ በገሃድ ለመፈረጅ መሞከሩም በሪፖርቱ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ መንግስት የመናገር-የመደራጀት-የመሰብሰብን መብት የሚተገብሩ ፖለቲከኞችናና ጋዜጠኞችን እንደሚያስር፣ እንደሚያሰቃይ፣ እንደሚያንገላታ፣ የሚገልጸዉ ሪፖርት ከፖለቲከኞች የመድረኩ አንዱአለም አራጌ ብሎም የኦሮሞን ማህበረስብ መብት በዲሞክራሲ ለማስከበር ከሚንቀሳቀሱ የኦሮሞ ተወላጆች በቀለ ገርባና ኦልባና ሌሊሳ ታስረዉ እየተሰቃዩ መሆናቸዉን፤ ተመሳሳይ በሆነ መልኩ ከጋዜጠኞች እስክንድር ነጋ፣ሪዮት አለሙና ሰለሞን ከበደ በእስር ይማቅቃሉ ሲልም ሪፖርቱ ያስረዳል።
መንግስት ነጻ-ፕሬስ እንዲከስም በሚያደርገዉ ከፍተኛ ጫና ጋዜጠኞች የእስርና የስደት ሰለባ
Source ECADF