(ከኢየሩሳሌም አርአያ)
ፓርቲው ለሁለት ሲሰነጠቅ በመለስ ዜናዊ ታማኝ ሆነው ከተመረጡት አንዱ የሆኑት ረዳኢ በፌዴራል የልዩ ተወርዋሪ ሃይል ሃላፊ ተደርገው መሾማቸውን ምንጮቹ አስታወሰዋል። ቀጥታ ተጠሪነታቸው ለጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ እንደነበር ሲታወቅ በመቀጠል የፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ሃላፊ ተደርገው ተሾሙ። በ1997-98 በዜጎች ላይ ለደረሰው የጅምላ ግድያና እስር እንዲሁም ስቃይ ከመለስ ትእዛዝ በመቀበል ሲያስፈፅሙ የነበሩት ረዳኢ መሆናቸውን ምንጮቹ አመልክተዋል።
በበርካታ ሰላማዊ ወገኖች ላይ ተመሳሳይ ግፍ ያስፈፅሙ እንደነበረ አክለዋል። ረዳኢ በ10 ሚሊየን የሚቆጠር ሃብት በሙስና እንዳከማቹ ምንጮቹ አረጋግጠዋል። ከስልጣን የተነሱት ለመለስ ታማኝ ስለነበሩ ነው ብለዋል ምንጮቹ። ረዳኢ ወደ አሜሪካ ለመምጣት ሃሳብ እንዳላቸው እዚህ ከሚኖሩ የቅርብ ወዳጃቸው የተገኘው ጥቆማ ያመለክታል።
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar