mandag 30. september 2013

ለግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል በኦስሎ ኖርዌ የተሳካ የገቢ ማሰባሰቢያ ተካሄደ


ለግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል የገቢ ማሰባሰቢያ በኖርዌ ኦስሎ ከተማ ሴፕቴምበር 28, 2013 ለመጀመሪያ ጊዜ ተካሂዶ በደማቅ ሁኔታ የተከናወነ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ከፍተኛ አመራር ኮማንደር አሰፋ ማሩ እና የግንቦት ሰባት ለፍትህ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሃፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እንዲሁም ከተለያዩ ሃገራት የተገኙ እንግዶች የተሳተፉበት ዝግጅት ነበር።

በዝግጅቱ መክፈቻ ላይ የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሃይሉ መዝሙር በወጣት ዘማሪያን የቀረበና ህዝቡም በከፍተኛ ስሜት የሃገር ፍቅር እያንገበገበውና ግማሹም በማልቀስ ስሜቱን የገለፀበት ዝማሬ ነበር። በመቀጠል የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጀት በኖርዌ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ዳዊት መኮንን የመክፈቻ ንግግር  ካደረጉ በኋላ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይሉ መድረኩን በመቀበል ስለድርጅታቸው ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ከህዝቡ የቀረበላቸውንም ጥያቄዎች በስፋት አስረድተዋል። አቶ አንዳርጋቸው ፅጌም ለታዳሚው በምስል የተደገፈ ሰፋ ያለ መረጃ ሰጥተው ክህዝቡም የቀረበላቸውን ጥያቄዎች ለህዝብ በሚገባና ግልፅ በሆን ሁኔታ አስረድተዋል።



በተጨማሪ የተለያዩ ቀስቃሽ ሙዚቃዎች፡ ጨረታዎች እንዲሁም ምግብና መጠጥ እንዲሁም የትጥቅ ትግል ለምን አስፈለገ በሚል ገላጭ የሆነ አጭር ድራማ ቀርቧል። በአንፃሩ ይህንን ዝግጅት እንዳይሳካ ለማድረግ የወያኔ ተላላኪዎች እንቅልፋቸውን አጥተው  ሙከራ ቢያደርጉም አይናቸው እያየ ጆሯቸው እየሰማ ዝግጅቱ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከፍተኛ የገቢ ማሰባሰቢያ ተደርጎ ዝግጅቱ በደማቅ ስነስርአት ተከናውኗል።  



ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር
ዲቦራ ለማ/ኖርዌ

የተቃውሞ ፓርቲዎች ሠላማዊ ሰልፍ በአዲስ አበባ


udj 5 19
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትኅ ፓርቲ ከ 33ቱ ፓርቲዎች ጋራ በመሆን ለዛሬ በመስቀል አደባባይ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በፖሊስ ክልከላ የአንድነት ጽ/ቤት በሚገኝበት ቀበና መካሄዱ ተገለፀ።
የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ሰልፉን ተከታትሎ ባደረሰን መረጃ መሰረት እጅግ በርካታ ሠላማዊ ሰልፈኞች ሠልፉን ለማከናወን ወዳቀዱበት መስቀል አደባባይ እንዳይሄዱ ፖሊስ መንገዱን በመዝጋት ተከላክሎዋል። ከ ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ጋ ያደረግነውን ቃለ መጠይቅ ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትኅ ፓርቲ ከ 33ቱ ፓርቲዎች ጋራ በመሆን ለዛሬ በመስቀል አደባባይ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በፖሊስ ክልከላ የአንድነት ጽ/ቤት በሚገኝበት ቀበና መካሄዱ ተገለፀ። የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ሰልፉን ተከታትሎ ባደረሰን መረጃ መሰረት እጅግ በርካታ ሠላማዊ ሰልፈኞች ሠልፉን ለማከናወን ወዳቀዱበት መስቀል አደባባይ እንዳይሄዱ ፖሊስ መንገዱን በመዝጋት ተከላክሎዋል። አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ በሰልፉ ወደ 80,000 የሚጠጉ ሰዎች መሳተፋቸውን የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እንደሚገምቱ ጠቅሷል። የዜና አውታሩ አያይዞም የመንግሥት ቃል አቀባይ ሬድዋን ሁሴን በሰልፉ የተገኙት በጥቂት መቶ የሚቆጠሩ እንደሆኑ መግለፃቸውንም ገልጿል።
Demonstration der äthiopischen Oppositions-Partei am 29.09.2013. zugeliefert von: Lidet Abebe copyright: DW/Y.G. Egziabher
ሰልፈኞቹ የጸረ-ሽብር ሕጉ ይሰረዝ፣ የታሰሩ የኅሊና እስረኞች ይፈቱ፣ የኢሕአዴግ መገለጫው ሙስና ነው፣ የሕዝቡ የመሬት ባለቤትነት ይረጋገጥ፣ መብትን መጠየቅ አሸባሪነት አይደለም፣ ፍትኅ እንፈልጋለን፣ ዲሞክራሲ እንሻለን የሚሉና ሌሎች በርካታ መፈክሮችንም በከፍተኛ ድምፅ ማሰማታቸው ታውቋል።
በሰልፉ ላይ ከቃሊቲ እስር ቤት የተላከው የአንዱዓለም አራጌን ጨምሮ ዝዋይ ከሚገኙ እስረኞች የተላከ መዕልክት በንባብ ቀርቧል። ሠልፉ በአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ንግግር በፓርቲው ጽ/ቤት መጠናቀቁ ታውቋል። (ፎቶና ዜና: DW)

ታላቅ ሰበር ዜና፤ በኖርዌ ለግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል የተደረገ የገቢ ማሰባሰቢያ በስኬት ተከናወነ!!!!!!!!!!

ዛሬ ሴፕቴምበር 28, 2013 በዓለም ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይልን ለመርዳት በኖርዌ ኦስሎ ከተማ የተዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም የህዝባዊ ሃይሉ ከፍተኛ አመራር ኮማንደር አሰፋ እና የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እንዲሁም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት በኖርዌ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ዳዊት መኮንንና ጥሪ የተደረገላቸ እንግዶችና ከተለያየ የአውሮፓና ስካንዴኔቪያን ሃገሮች መጡና በጣም በርካታ የሆኑ በኖርዌ በሚኖሩ ከተለያየ ከተማ የመጡ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በታላቅ ወኔና የሃገር ፍቅር ስሜት በስኬት ተከናወኖ አመሸ።

በዝግጅቱ ላይ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሀይሉ አመራር ስለድርጅታቸው በሰፊው ህዝቡን ያስደሰተ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ከታዳሚው የቀረባላቸውንም ጥያቄዎች በስፋት በማብራራት ለታዳሚው ከፍተኛ ግንዛቤ አስጨብጠዋል። በተመሳሳይ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በምስል የተደገፈ ከፍተኛ ማብራሪያ ሰጥተው ከህዝብ የቀረበላቸውን ጥያቄዎች ሰፋ አድርገው አስረድተዋል።

በአንፃሩ እጃችን እረጅም ነው ብለው የሚያስቡ ጠባብ አስተሳሰብ ያላቸው የወያኔ ተላላኪ ቡድኖች ዲሞክራሲ ባለበት በኖርዌ ምድር መጥተ እንኳን የማይቀየሩ አምባገነኖች እዚህም ዝግጅታችን እንዳይሳካ ለማበላሸት እንቅልፍ ሳይተኙ የሃሰት ፕሮፓጋንዳቸውን እየነፉ ህዝብ ለማደናገር የአሸባሪ ድርጅት ለመርዳት የገቢ ማሰባሰቢያ ሊያደርጉ ነበር ነገር ግን ፕሮግራሙ ተሰረዘ በማለት ዜና ቢያሰራጩም እኛ ግን እየረዳን ያለነው የግንቦት7 ህዝባዊ ሃይል በየትኛውም አለም  በአሸባሪነት መዝገብ ውስጥ ያልተመዘገበ ድርጅት መሆኑን የኖርዌ ፕሮፌሰር በሃገሪቱ ውስጥ ለሚታተም አንድ  ጋዜጣ አስተያየታቸውን የገለፁ ሲሆን በእለቱም ዝገጅቱ በደማቅ ሁኔታ ተከናውኖ ከዚህ ቀደም በየተኛውም የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮገራም ያልታየ ከፍተኛ የገንዘብ ገቢም ተደርጓል።

በአጠቃላይ በዝግጅቱ ላይ የተለያዩ ጨረታዎች፤ ቀስቃሽ ሙዚቃ፤ ባህላዊ ምግብና መጠጥ እንዲሁም የተለያዩ ቁሳቁሶች ለሽያጭ ቀርበው የነበረ ሲሆን በተጨማሪም የትጥቅ ትግል ለምን አስፈለገ በሚል አጭር ገላጭ ድራማ ቀርቦ ህዝቡን በጣም አስደስቷል። በዝግጅቱ መክፈቻና መዝጊያ ላይም የህዝባዊ ሃይሉ መዝሙር ላንቺ ነው ሃገሬ ላንቺ ነው የሚለው በህዝቡ ተዘምሮ ዝገጅቱም እኩለ  ለሊት በድምቅት ተጠናቋል፡፡

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ሞት ለወያኔ
ሄለን ንጉሴ/ኖርዌ

torsdag 26. september 2013

‹‹ ደረጃ ዜሮ ›› በገለልተኛ ጥናት ያልታገዘ የፀረ ሙስና ትግል










‹‹ ደረጃ ዜሮ ›› በገለልተኛ ጥናት ያልታገዘ የፀረ ሙስና ትግል

የዛሬ የጽሑፌ ማጠንጠኛ በአገሪቱ ያለው የፀረ ሙስና ትግል በጥናትና ምርምር፣ ብሎም በሕዝብ ምክክርና ተሳትፎ ገና ያልዳበረ መሆኑን መሞገት ነው፡፡ መንግሥት በተለይም ‹‹የሕዝቡ ተሳትፎ ጨምሯል›› ቢልም በሌላው ዓለም ኅብረተሰቡ ሙስናን ከሚታገልበት ሁኔታ አንፃር እጅግ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ገለልተኛ የዘርፍ ተቋማትና ምሁራን በጥናት ላይ የተመሠረተ የፀረ ሙስና ትግል ተሳትፏቸው ‹‹ዜሮ ደረጃ›› ላይ የሚገኝ የሚባል ነው፡፡ ምክንያቱ ምንድን ነው?
 http://africlaw.files.wordpress.com/2013/07/current-efforts-to-fight-corruption-are-spear-headed-by-the-federal-ethics-and-anti-corruption-commission-of-ethiopia-but-it-might-not-deliver-the-much-desired-outcome.jpg?w=590&h=296

በጥናት ላይ የተመሠረተ ትግል የተሟላ ውጤት ያስገኛል
ከስድስት ወራት በፊት ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ያወጣው አንድ መረጃ በስፔን የክልል ፕሬዚዳንቶችንና ሚኒስትሮችን ጨምሮ ከ300 በላይ የሚሆኑ ባለሥልጣናት በሙስና መዘፈቃቸውን ይፋ አደረገ፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ማሪያኖ ራሆይ መንግሥት በሙስና እንዲታማ በዋናነት አስተዋጽኦ አድርገዋል የሚባሉት የቀድሞው ሕዝባዊ ፓርቲ ዓቃቤ ንዋይ ሉዊስ ባርሲናስ ነበሩ፡፡ 22 ሚሊዮን ዩሮ የሚደርስ ገንዘብ በስውስ ባንክ ደብቀው በማስቀመጣቸው ማለት ነው፡፡ ይህና ሌሎች በርካታ የሙስና በደሎች መፈጸማቸውን ያረጋገጠው ግን ጠንካራው ጥናትና ጥርስ ያለው የሕትመት ሚዲያ ነበር፡

Ethiopia: Beyond the Hubris of Evil

Ethiopia: Beyond the Hubris of Evil September 22, 2013
by Alemayehu G. Mariam
When I wrote a commentary on the plight of the imprisoned 32-year old Ethiopian journalist Reeyot Alemu last April, I titled it “The Audacity of Evil in Ethiopia.” At the time, the Committee to Protect Journalists (CPJ) had sent a letter to the “Minister of Justice” of the ruling regime in Ethiopia pleading medical care for Reeyot and urging them to spare her from a threatened solitary confinement. In that commentary, I explained why I was compelled to “stray from my professional fields of law and politics” to moral philosophy.

In this commentary, I am again compelled to indulge in philosophical musings on the hubris of evil. I am prompted once again by a statement of the Committee to Protect Journalists issued last week protesting the decision by the ruling regime to impose severe visitor restrictions on Reeyot.  CPJ “called upon the Ethiopian authorities to lift these latest restrictions and allow Reeyot Alemu to receive all visitors… She is a journalist, not a criminal, and should not be behind bars.”

Reeyot began a hunger strike to protest an order by regime officials
Reeyot began a hunger strike to protest an order by regime officials to pre-clear a list of her prison visitors. “In retaliation for the hunger strike, authorities forbade her from having any visitors excluding her parents and priest.” She was subsequently told that “she could receive any visitors except for her younger sister and her fiancé, journalist Sileshi Hagos [who had spoken publicly about the visitor exclusion order]… Sileshi was detained for four hours at the prison later that day when he attempted to visit Reeyot.”

እንደ ቆራጥ ንስር ፓይለቶቹ…


ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያውያን ዘንድ ዋና የመነጋገሪያ አርዕስት የነበረው አራት የአየር ሃይል አብራሪዎችና አስልጣኝ መኮንኖች ከዘረኞቹና ከዘራፊዎቹ ጎራ ወጥተው ወደ ነፃነት ታጋዮች ጎራ የመቀላቀላቸው ጉዳይ ነበር። እነዚህ ቆራጥና አገር ወዳድ አብራረዎች የወሰዱት እርምጃ ወገንን የሚያኮራና ከፍተኛ ጀግንነትን የሚጠይቅ ትልቅ ውሳኔ ነው።ይህ ውሳኔ ሰው ባጣች አገር፤ጀግና ባጣች አገር፤ለአገር ለወገን ተቆርቋሪ ባጣች አገር ውስጥ ትልቅ ተስፋ ሰጪ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ በያለበት በተለያየ መንገድ ይህን የጀግና ውሳኔ የወሰኑ ልጆቹን እያደነቀም እያመሰገነም ይገኛል::
የግንቦት ሰባት ንቅናቄም ይህን የጀግና ውስኔ የወሰኑ ወንድሞቹን እንኳን ተወለዳችሁ፤ እንኳንም ተማራችሁ፤ እንኳንም ወደ ነፃነቱ ትግል ተቀላቀላችሁ እያለ ደስታውንና ለጀግኖቹ ያለዉን ከፍተኛ አክብሮት ይገልፃል። ውሳኔያችሁ ከፈርዖን ቤተ-መንግስት ምቾት ይልቅ ከህዝቤ ጋር መሰደደ ይሻለኛል ያለውን የታላቁን ሰው የሙሴን ውሳኔ ይመስላልና የወሰዳችሁትን ትክክለኛ እርምጃ ትውልድ ምን ግዜም አይረሳዉም።
የእነዚህ ቆራጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ልጆች፣ ሙያና ችሎታ ስጋዊ የሆነ ፍላጎታቸውን ለማርካት ከበቂ በላይ ነው።ከዘረኞቹና ከቃየላውያኑ ቡድኖች ጋር እየተሞዳሞዱ ለመኖርም የሚሳናቸው አልነበሩም።ሆኖም ግን ዘረኞቹ(ህወሃቶች) የሚፈፅሙትን ግፍ ተሸክመው ፤ብኩርናቸውን ሽጠው እና ከሰው ተራ ወርደው ለመኖር ሂሊናችው አልፈቀደላቸውም።ለሚበላና ለሚጠጣ ከንቱ ነገር ብለው ጥቂት ዘረኞችን ተሸክሞ ከመኖር ይልቅ የነፃነቱን መንገድ መርጠዋልና ጀግኖች ብለን ብናወድሳቸው ተገቢ ይሆናል። እንዲህ ዓይነቱን ውሳኔ የሚወስን ሃሞተ ኮስታራ ጀግና እንጂ ሌላ አይደለም።
አሁንም ለራሳችሁ ክብር ያላችሁና ተመሳሳይ እርምጃ ለመዉሰድ በዝግጅት ላይ የምትገኙ የአገር መከላከያ አባላት እንዳላችሁ እናውቃለን። ቅምጥሎቹ ጄኔራል ተብየዎች ከድሃ ወገኖቻችሁ ላይ የዘረፉትን ዘርፈው አገሪቷን ጥለው መሄድ ጀምረዋል። ቀሪዎችም የዘረፉትን የድሃ ንብረት ወደ ውጪ አገር እያሸሹ እንደሆነም ይታወቃል።በአጠቃላይ በእናንተ ምርኩዝነት አገራችንን እያፈራረሷት፤ህዝቧንም እያወረዷት ነው።የህዝቡም መከራና እሮሮ ተወርቶ የሚያልቅ አይደለም።እንዲህ አይነቱን ግፍና በደል እያዩ ከንፈር መምጠጥ እያበቃ ነው።እንግዲህ አሁን እኔ ብቻየን ምን አደርጋለሁ የሚባልበት ግዜ እያለፈ ነው።ጋሻ መከታ እና የኋላ ደጀን የሚሆኗችሁ ብዙ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዉያን በየቦታው አሉ።ብትወድቁ የሚያነሷችሁ፤ብትደሙ ደማችሁን የሚያብሱላችሁ፤ብትሰው መስዋእትነታችሁን ለትውልድ የሚዘክሩላችሁ ወገን አለላችሁ።አትፍሩ። ከዘረኞቹ መንደር ወጥታችሁ የነፃነቱን ትግል እንድትቀላቀሉ ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርብላችኋለን።
ህውሃት ማለት የዘራፊዎች እና የጨካኝ ነፍሰ ገዳዮች ስብስብ መሆኑን ያለምንም ጥርጥር ማመን አለባችሁ።ህወሃት ስንቱን አርዶ፤ስንቱን ገድሎ፤ስንቱን አጥፍቶ፤የስንቱን ኑሮ በትኖ፤ስንቱን ዘርፎ ባዶ እጁን አስቀርቶ በትረ ስልጣኑን እንደያዘ ምስክር የሚያስፈልገን አይደለም።
የህውሃት ዘረኝነትና ዝሪፊያ የቆጨህ እና ለራስህ ክብር ያለህ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ተነስተህ ትግሉን ተቀላቀል።እነዚህን ግፈኞች የሚፈፅሙትን በደል እያዩ ዝም ማለት ግፉን ከመደገፍ ተለይቶ የሚታይ አይደለም።እናንተ ለራሳችሁ፤ ለወገናችሁና ለአገራቸችሁ ክብር ያላችሁ ዜጎች ዝም በማለታችሁ ህወሃቶች ዝምታችሁን እንደ በጎ ፈቃድ ቆጥረውት የግፍ ሰይፋቸውን ወደ ሰገባው ሊመልሱ ፈቃደኞች አልሆኑም።በማን አለበኝነታችውም ፀንተው ቆመዋል።እነዚህን ግፈኞች በቃ ለማለት ግዜው ደርሷልና የነፃነቱን ትግል ሳትዘገዩ አሁኑኑ ተቀላቀሉ።
እኛም ወደ ነፃነት ትግሉ እንድትቀላቀሉ ጥሪ ስናደርግላችሁ ለአገራችን ክብርና ለወገኖቻችን በሰላም መኖር ስንል ቆርጠን የተነሳን መሆናችንን ልንገልጽላችሁ እንወዳለን።የግንቦት ሰባት ንቅናቄ በምንም ሁኔታ በዘረኞች እጅ ተንቆና ተዋርዶ መኖርን አይቀበልም።እንዲህ ዓይነቱን ውርደት ተቀብሎ ለመኖር ሰው መሆናችን ይከለክለናል።እነዚህን ዘራፊዎች ተሸክመን ከመኖር ከነፃነታችን ጋር አያቶቻችን በተሰውበት ተራራ ላይ ቆመን መሰዋትን እንመርጣለን።አሁን ተነስተናልና የሚያቆመን የለም። እግዚአብሄርም መንገዳችንን ያከናውንልናል። ኑ ሀገርን ለማዳን የነጻነት ትግሉን ጎራ ተቀላቀሉ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

ESAT Special Ginbot 7 Meeting in DC Sep 22, 2013


http://ethsat.com/video/esat-special-ginbot-7-meeting-in-dc-sep-22-2013-part-1/

http://ethsat.com/video/esat-special-ginbot-7-meeting-in-dc-sep-22-2013-part-2

http://ethsat.com/video/esat-special-ginbot-7-meeting-in-dc-sep-22-2013-part-3

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀ መንበር አንዱአለም አራጌ የአመቱ ሰው ተብሎ በመሰየሙ የተሰማቸውን ደስታ ገለጹ

ትርጉም  በግርማ ሞገስ

ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀ መንበር አንዱአለም አራጌ የአመቱ ሰው ተብሎ በመሰየሙ የተሰማቸው ደስታ ለመግለጽ በእንግሊዘኛ የፃፉት መልዕክት በጥያቂያቸው መሰረት ከሞላ ጎደል እንደሚከተለው ቀርቧል።


ቅዳሜ መስከረም 4 ቀን 2006 ዓ.ም. 
Saturday, September 14, 2013

“ዘሐበሻን እና ሌሎች ሚዲያዎችን የመድረስ አቅም ያላቸው እህቶቻችን እና ወንድሞቻችን አንዷለም አራጌን የአመቱ ሰው አድርገው መምረጣቸውን መስማቴ ታላቅ ደስታ ሰጥቶኛል። አንዷለም ለህዝቡ እና ለአገሩ ብዙ ያበረከተ እና የተጠየቀውን መስዋዕት ሁሉ ካለ ምንም ስስት የከፈለ እና በመክፈል ላይ የሚገኝ ድንቅ ግለሰብ በመሆኑ ለአንዷለም ይኽን እውቅና በመለገሳችሁ ላመሰግናችሁ እወዳለሁ።

እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1998 ዓ.ም. ከእስር ቤት ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ደግሞ መድረክን ወደ ህብረት ከፍ ለማድረግ የፖለቲካ ፕሮግራም እና መተዳደሪያ ደንብ አብረን መቅረጽ ከጀመርንበት ጊዜ ጀምሮ አንዷለምን አውቀዋለሁ። ብዙ ፍሪያማ አሳቦችን ለግሷል። መድረክ ወደ ግንባር ደረጃ እንዲደርስ ለማድረግም ካለምንም መታከት ሰርቷል። አንዷለም አንድነት ፓርቲን ወክሎ በመድረክ ስራ አስኪያጅ ኮሚቴ ወስጥ በነበረበት ጊዜ ለመድረክ ፕሮጀክት መሳካት ብዙ ከጣሩት የአንድነት ሰዎች ውስጥ አንዱ ነበር። ለወቅቱ የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ አክብሮት ነበረው። እጅግ ቀና የሆነ የስራ ግንኙነት ነበራቸው። ያኔ እንደማውቀው እና ዛሬም እንደሚመስለኝ አንዷለም መድረክን በሚመለከት ከአንድነት ከሚሰሙ አሉታዊ ድምጾች ጋር አይስማማም። ቀደም ሲልም በዚህ ጉዳይ ላይ ጽኑ ክርክሮች አድርጓል።

አንዷለም ከመኢአድ እና ያኔ ከአንድነት ተነጥለው ከሄዱት ወገኖች (ዛሬ ሰማያዊ ፓርቲ) ጋር ውህደት እንዲደረግ ይፈልግ ነበር። በዚህ አቅጣጫ አንዷለም የአንድነት ፓርቲን ስራ አስኪያጅ ኮሚቴ አግባብቶ ወይዘሮ ላቀች ደገፉ እና አቶ ተመስጌን ዘውዴ ያሉበትን የድርድር ኮሚቴ ፓርቲው እንዲመሰርት አድርጎ ነበር። ሁለተኛ እስር እስከተበየነበት ጊዜ ድረስ ለዚህ ጉዳይ መሳካት በመስራት ላይ ነበር አንዷለም።

አንዷለም ቁርጠኛ የሰላማዊ ትግል ተዋጊ ነበር። የማህተማ ጋንዲ እና የማርቲን ሉተር ተከታይ። የፖለቲካ እንቅስቃሴዎቹ የሚመሩት በእነዚህ ሁለተ ሰዎች ትምህርቶች ነበር። አንዷለምን ሽብርተኛ ነው ወይንም ከሽብርተኞች ጋር ግንኙነት ነበረው ብለው የሚያስቡ ሰዎች ካሉ አዕምሮዋቸውን የሳቱ እና እራሳቸው ሽብርተኞች ናቸው።

አንዷለም የአንድነት ጸሐፊ እና የአንድነት ህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ሊቀመንበር በነበረበት ጊዜ ለድርጅቱ ስኬት ለሊት እና ቀን ሰርቷል።

ባለቤቱን እና ሁለት ልጆቹን ይወድ ነበር። ቀኑን እና ምሽቱን ለአንድነት ሲሰራ ውሎ ምሽት ላይ ወደ ቤተሰቡ ነበር የሚሄደው። ወደ መዝናኛ ቦታዎች ከመሄድ ፈንታ።

ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀ መንበር
ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀ መንበር

የግል ህይወቱን በሚመለከት፣ አንዷለም የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶችን በንጹሕ ልቦና የሚከተል መንፈሳዊ ሰው ነው። አንዷለም “ ግራ ፊትህን በጥፊ ለመታህ ሰው ቀኝ ፊትህን ስጠው። ሌሎች በአንተ ላይ እንዲፈጽሙብህ ያማትፈልገውን አንተም በሌሎች ላይ አትፈጽም።” የሚሉት የእየሱስ ክርስቶስ ትምህርቶች ተከታይ ሰው ነው። ሰው አስቀይሞ ወይንም ተሳድቦ አያውቅም። ሲሰደብም መልሶ አይሳደብም። አይበቀለም አንዷለም። ምክርን እና ማጽናናትን ለሚሹ ሁሉ አንዷለም ጊዜ ነበረው።

አንዷለም አዕምሮ-ክፍት እና ግልጽ ሰው ነው። የማዳመጥ ልዩ ችሎታ አለው።

አንዷለምን “የአመቱ ሰው” ብላችሁ መምረጣችሁ ትክክለኛ ውሳኔ ነው። ይገባዋል። ለሁላችሁም ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።


ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣

የአንድነት ሊቀመንበር”