søndag 25. oktober 2015

የኢሳት 5ተኛ አመት በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ በተሳካ ሁኔታ ተካሄደ!


 ዲቦራ ለማ/ኖርዌ

አርቲስና አክቲቪስት ታማኝ በየነ እንዲሁም ታዋቂው የኢሳት ጋዜጠኛ አፈወርቅ አግደው በተገኙበት ኢሳት የተቋቋመበትን የአምስተኛ አመት በአል በደማቅ ሁኔታ በኦክቶበር 24፣ 2015 በኦስሎ ከተማ ተካሄደ። በዝግጅቱ ላይ ከተለያየ የኖርዌ ከተማዎች የመጡ በርካታ ታዳሚዎች ተገኝተውበታል።



ዝግጅቱ በኖርዌ የሚኖሩ ታዳጊዎች ኢሳት የተመለከተ ዝማሬ አቅርበው ታዳሚውን ያስደመሙ ሲሆን በመቀጠል በኖርዌ የኢሳት ኮሚቴ ሊቀመንበር የእንኳን ደህና መጣችሁና የመግቢያ ንግግር በማድረግ ፕሮግራሙን ጀምሯል። በመቀጠል የተለያዩ አዝናኝና አስተማሪ መጣጥፎችና ግጥሞች እንዲሁም አጭር ጭውት በዝግጅቱ ላይ ቀርቧል። ለገቢ ማሰባሰቢያው የሚውል የምግብና መጠጥ ሽያጭ፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች ሽያጭ እንዲሁም የትኬት ሽያጮች ተካሂዷል።

ጋዜጠኛ አፈወርቅ አግደው የሚያስደንቅ ስራውን በመድረክ ያቀረበ ሲሆን አርቲስት ታማኝ በየነም የተለያዩ መረጃዎችን ለህዝቡ አቅርቧል። የጨረታው ሰአት ሲደርስ ጨረታውን አርቲስት ታማኝ በየነ የመራ ሲሆን በጨረታው ላይ በርካታ ተሳታፊዎች ተሳትፈዋል። የጨረታውን ዋንጫ ያቀረቡት በኖርዌ በርገን ከተማ ነዋሪ የሆኑ የኢሳት ቤተሰቦች ሲሆኑ በመድረክላይም ኢሳት ይቀጥላል የሚል የራሳቸውን ዝማሬ አቅርበዋል።

ከጨረታ፣ ከምግብና መጠጥ ሽያጭ፣ እንዲሁም ከትኬት ሽያጭ እንዲሁም ከተለያዩ ነገሮች ሽያጭ ለኢሳት ከፍተኛ ገቢ ተገኝቷል። ዝግጅቱ በደማቅ ሁኔታ በኖርዌይ የሰአት አቆጣጠር ከምሽቱ 23፡00 ተጠናቋል።



ኢሳት በእኛ ድጋፍ ይቀጥላል!!

tirsdag 20. oktober 2015

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ለሁለተኛ ጊዜ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት አስመረቀ

October 20, 2015
የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ
Professor Berhanu Nega with Patriotic Ginbot7 fighters
አርበኞች ግንቦት 7 በሁለት ድርጅቶች ማለትም በኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር እና በግንቦት 7 ንቅናቄ ውህደት ጥር 2 ቀን 2007 ዓ.ም ከተመሰረተ በኋላ ከትናትና በፊት እሁድ ዕለት ጥቅምት 7 ቀን 2008 ዓም ለሁለተኛ ጊዜ ብዛት ያላቸውን አርበኛ ታጋዮች ለሦስት ወራት አሰልጥኖ አስመርቋል፡፡
እነዚህ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሁለተኛ ዙር ተመራቂ አርበኛ ታጋዮች ለሦስት ተከታታይ ወራት የተሰጣቸውን የፖለቲካ፣ የወታደራዊ እና ሌሎች ተያያዥ የሆኑ የመረጃና ደህንነት ትምህርቶችን በሚገባ ወስደው በሁሉም መስክ አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ ነው ሊመረቁ የቻሉት፡፡
እጅግ በጣም ደማቅ በሆነ ስነ-ስርዓት በተከናወነው የምረቃ በዓል ላይ ከተለያዩ ቦታዎች ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች የታደሙ ሲሆን የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር አርበኛ ታጋይ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የድርጅቱ የትምህርትና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ታጋይ ተስፋሁን ተገኝ ንግግር በማሰማት ለተመራቂ አርበኛ ታጋዮች መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ከውህደቱ ኋላ የመጀመሪያውን ዙር ሰልጣኞች ያስመረቀው ግንቦት 2 ቀን 2007 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል፡፡
Patriotic Ginbot7 fighters

onsdag 14. oktober 2015

በእነ ሀብታሙ አያሌው ላይ ተረኛ ችሎት የወሰነውን ይግባኝ ሰሚ ሻረው

የአቃቤ ህግ ይግባኝ ያስቀርባል ወይስ አያስቀርብም የሚለው ጥቅምት 17/2008 ይወሰናል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ እንዲሰናበቱ የተበየነላቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ላይ አቃቤ ህግ ይግባኝ ጠይቆ በተረኛ ችሎት ይግባኙ ያስቀርባል ቢባልም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ይህንን ውሳኔ በመሻር ያስቀርባል ወይስ አያስቀርብም የሚለውን ለመበየን ለጥቅምት 17/2008 ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
Habtamu abrhayeshiwas daniel
ዛሬ ጥቅምት 3/2008 ዓ.ም የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የቀረቡት የፓርቲ አመራሮቹ ሀብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ዳንኤል ሺበሽ እና አብሯቸው ይግባኝ የተጠየቀበት አብርሃም ሰለሞን ዛሬ የቃል ክርክር እንደሚያደርጉ የሚጠበቅ የነበር ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ ግን በነሀሴ 15/2007 ዓ.ም ተረኛ ችሎት ይግባኙ ያስቀርባል ያለውን ውሳኔ ወደ ጎን በመተው አቃቤ ህግ የይግባኝ አቤቱታውን እንደገና እንዲያሰማ አድርጓል፡፡
በመሆኑም አቃቤ ህግ የስር ፍርድ ቤት በአቃቤ ህግ የቀረቡትን የቴክኒክና የሰነድ ማስረጃዎች ይዘት በአግባቡ ሳይመረምር ውሳኔ ስለሰጠብን ውሳኔው አግባብ ስላልሆነ ይግባኝ ሰሚ ችሎቱ እንዲመረምርለት ጠይቋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ይህንኑ የይግባኝ አቤቱታ መርምሮ ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 17/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በሌላ በኩል በነጻ እንዲሰናበቱ የተበየነላቸው ተከሳሾች እስካሁን በእስር ላይ የቆዩበት ምክንያት አግባብ ስላልሆነ አቤቱታ እንደሚያቀርቡ ተከሳሾች ገልጸዋል፡፡ እስካሁን በእስር ላይ ሊቆዩ የቻሉት ተረኛ ችሎቱ በሰጠው እግድ መሆኑ ቢገለጽም፣ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ግን አቤቱታው እንዲቀርብ ፈቅዷል፡፡ ተረኛ ችሎቱ ነሀሴ 15/2007 ዓ.ም ብይኑን ሲሰጥ ተከሳሾች ችሎት ሳይቀርቡ እንደነበር ይታወሳል፡፡
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47406#sthash.fJjDuUvj.dpuf

tirsdag 13. oktober 2015

ሐብታሙ አያሌው በኩላሊት ጠጠር መታመሙ ተገለጸ * እነ አብርሃ ደስታ ነገ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

  • 27
     
    Share
habtamu ayalew
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47386#sthash.GZ4e0GZW.dpuf
(ዘ-ሐበሻ) በ እስር ቤት የሚገኘው ታዋቂው ፖለቲከኛ ሃብታሙ አያሌው ዛሬ በድንገተኛ ህመም ዘውዲቱ ሆስፒታል ተወስዶ እንደነበር ተዘገበ:: በአዲስ አበባ የሚገኙ የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንዳሉት ሃብታሙ ከ እስር ቤት ወደ ዘወዲቱ ሆስፒታል የተወሰደበት ምክንያት በሁለቱም ጎኖቹ ላይ የህመም ስሜት ስለተሰማው ነበር:: የዘውዲቱ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች ምርመራ ካደረጉለት በኋላ ህመሙ የኩላሊት ጠጠር መሆኑን ለባለቤቱ ወ/ሮ ቤተልሄም መናገራቸውን እነዚሁ ምንጮች አብራርተዋል:: ሃብታሙ ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የተመለሰ ሲሆን በነገው ዕለትም ፍርድ ቤት እንደሚቀርብ ተገልጿል:: ከሃብታሙ አያሌው ጋር አብረው የተከሰሱትና በቅርቡ በከፍተኛው ፍርድ ቤት በነፃ የተለቀቁት አብርሃ ደስታ; ዳንኤል ሺበሺና የሺዋስ አሰፋም በነገው ዕለት አቃቤ ሕግ ይግባኝ በጠየቀባቸው ክስ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀርበው የቃል ክርክር ያደርጋሉ ሲሉ የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል:: 


søndag 4. oktober 2015

ኢሳት በእኛ ድጋፍ ይቀጥላል!!


ኦክቶበር 2, 2015
ዲቦራ ለማ/ኖርዌ/

አለማችን አሁን ያለችበት ዘመን በከፍተኛ  ደረጃ መረጃ ከአንዱ ወደ አንዱ በየሰከንዱ እየፈሰሰ አለምን ወደ አንድ ጎራ አምጥቶ የመረጃን ጠቃሚነት እያየን የመጣንበት ጊዜ ነው። መረጃ የአንድን ሀገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፓለቲካዊ እንቅስቃሴን ለማዳበር ከፍተኛውን ሚና ይጫወታል።

እንደሀገራችን ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት ደግሞ በተቃራኒው መረጃ ለህዝብ እንዳይደርስ የመረጃ መረቦችን በሙሉ በመበጣጠስና በማገድ ትክክለኛ መረጃ ለህዝብ እንዳይደርስ ሲከላከሉ እናያለን። በሀገራችን ኢትዮጵያ ያለው የመረጃ ምንጭ አንድ የገዥው ፓርቲ ልሳን የሆነው የኢትዮጵያ ቴሌቪዝንና ራዲዮ ሲሆን ሌሎችም የስርአቱ አቀንቃኝ የሆኑ እንደ ሬዲዮ ፋና ያሉ የግል ልሳናት አሉ። እነኚህ የወያኔ ልሳኖች አርባ ስምን ሰአት ያለምንም እፍረት የስርአቱን ፕሮፓጋንዳ ሲያሰራጩ ውለው ያድራሉ።
ህዝቡ ትክክለኛ መረጃ እንዳያገኝ ከፍተኛ ጫና በማሳደርና የህዝቡን ንብረት በመዝረፍና ህዝቡን ጦም በማሳደር በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በመክፈል ትክክለኛ መረጃ እያቀረበልን የሚገኘውን የኢሳትን ጣቢያ በተደጋጋሚ በማፈን ስርጭቱን ለማቋረጥ ወያኔ ብዙ ሙከራ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል።

ሆኖም ግን ኢሳት በህዝብ ድጋፍ ዛሬም ትክክለኛ መረጃን እያደረሰ የህዝብ አይንና ጆሮ ሆኖ ቀጥሏል። አምባገነኑ የወያኔ ስርአት ትክክለኛ መረጃን ለህዝብ የሚያቀርቡ ጋዜጠኞችንና ፀሀፊዎችን በእስር በማንገላታትና ከሀገር በማሰደድ መረጃን ሊያጠፋ ቢሞክርም ኢሳት ግን ዛሬም ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን ጨምሮ በሀገሪቱ ላይ የሚሰሩ ወንጀሎችን በማጋለጥ ለህዝቡ መረጃን እያቀረበ ይገኛል።

ኢሳት በኢትዮጵያ ከፍተኛ ተደማጭነት ያለውና አንድ ብቸኛ ትክክለኛ መረጃ አቅራቢ ተቋም ሆኖ በህዝብ ድጋፍ የሚንቀሳቀስ የህዝብ ሀብት ነው። ኢሳት በዚህ መልኩ በብዙ መሰናክሎች ውስጥ አልፎ  እነሆ ዛሬ 5ተኛ አመቱን በተለያዩ ሀገራት እያከበረ ይገኛል። በኦክቶበር  24, 2015 ደግሞ የኖርዌ ዋና ከተማ በሆነችው ኦስሎ ኢሳት 5ተኛ አመቱን በከፍተኛ ሁኔታ ለማክበር በዝግጅት ላይ ይገኛል። በመሆኑም በኖርዌ በተለያዩ ከተሞች የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ወደዚህ ዝግጅት ተጋብዛችኋል።

የአምባገነኖችን እድሜ ለማሳጠርና ዲሞክራሲያዊ መንግስት ለመመስረት ትክክለኛ መረጃ ለሀገራችን ህዝብ ወሳኝ በመሆኑ ኢሳት እንዲቀጥል የሁላችንም ተሳትፎ አስፈላጊ በመሆኑ በስፍራው ተገኝተን የበኩላችንን አስተዋፅኦ እናድርግ ብዬ ጥሪዬን አቀርባለሁ።



መረጃ ኃይል ነው


በእኛ ድጋፍ ኢሳት ይቀጥላል!!!!

ድርጅታችንን እናጠንክር፤ በጽናት እንታገል!

ድርጅታችንን እናጠንክር፤ በጽናት እንታገል!
October 4, 2015
def-thumb“የአርበኞች ግንቦት 7 አባል በመሆኔ እኮራለሁ” እያሉ በአገዛዙ የይስሙላ ችሎት ሳይቀር በድፍረት የሚናገሩ ወጣቶች ተፈጥረዋል። ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲ፣ ለእኩልነትና ለሀገር አንድነት መስዋዕትነት መክፈል የሚያኮራ ተግባር መሆኑ በተግባር የሚያሳዩ ወጣቶች መጥተዋል፤ አሁን በርካቶችም እየመጡ ነው። ወያኔ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በማኅበረሰባችን ውስጥ የዘራው የፍርሀትና የአድርባይነት ስሜት በራሱ በወያኔ የአገዛዝ ዘመን ተወልደው ባደጉ ወጣቶች እየተናደ፤ በምትኩ ሊጠፋ ተቃርቦ የነበረው የአገር ፍቅርና የአርበኝነት ስሜት እያንሰራራ ነው።
ቅንነት፣ ሀቀኝነት እና ጽናት ከተጣሉበት ጉድጓድ አቧራቸውን አራግፈው እየተነሱ ነው። በማኅበረሰባች ውስጥ ትልቅ የስነልቦና አብዮት እየተካሄደ ነው።
ከስነልቦና ለውጡ ጋርም በተግባር የአገር አድን ሠራዊትን የመቀላቀል ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ቁጥር በከፍተኛ መጠን እየጨመረ ነው። ወጣቶች የአገራቸው ባለቤት መሆናቸው ተገንዝበው የፓለቲካ ሥርዓት ለውጥ ለማምጣት በቁርጠኝነት መነሳታቸው ተስፋ ሰጪ ነገር ነው።
አርበኞች ግንቦት 7 በዚህ የለውጥ ወቅት ውስጥ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ አጽንዖት ልንሰጣቸው ስለሚገቡ የድርጅትና የሥነሥርዓት (ዲሲፕሊን) አስፈላጊነት ላይ የጋራ ግንዛቤ መያዝና በተግባርም መተርጎም አስፈላጊ ነው ብሎ ያምናል።
ወጣቶች ትግሉን ለመቀላቀል መሻታቸው መልካም ነገር ነው። ሆኖም ግን በድንገት ብድግ ብለው መንገድ ከመጀመር ይልቅ ከሚያምኗቸው ወዳጆቻቸው ጋር የመሠረቱት፤ ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋርም ትስስር የፈጠረ ስብስብ አካል ሆነው መቆየታቸው እጅግ አስፈላጊ ነው።
በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ሆኖ የሚስጢር ድርጅት ማዋቀር አስቸጋሪ መሆኑ የማያጠራጥር ቢሆንም የማይቻል ነገር ግን አይደለም። ወጣቶቻችን በአምባገነን ሥርዓት ውስጥም ሆነው በዲሲፕሊን የታነፀ ድርጅት የመፍጠርን ክህሎት መላበስ ይገባቸዋል። ይህንን ማድረግ ስንችል ነው የህወሓትን ፀረ-አገርና ፀረ-ትውልድ ተግባር ማክሸፍ የምንችለው። ትግሉን በሁሉም የኢትዮጵያ ግዛቶች ማቀጣጠል የምንችለው በየአካባቢው የተደራጀ የለውጥ ኃይል ሲኖረን ነው። ስለሆነም የምስጢር የተደራጀ አካል በየመኖሪያና የሥራ አካባቢዎቻችን ሁሉ እንዲኖር ማድረግ ከአጣዳፊ ሥራዎቻችን አንዱ እናድርገው።
ሁለተኛው ነጥብ ሥነሥርዓትን የሚመለከት ነው። ሥነሥርዓት ከሌለ ድርጅት የለም። የህወሓት አገዛዝ ያሳደረብን ጎጂ የባህል ተጽዕኖ ከባድ በመሆኑ ራሳችንን በሥነሥርዓት ለማነጽ መልፋት ይጠበቅብናል። አገራችንና ራሳችንን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ አውጥተን የተሻለ ሥርዓት ማምጣት የምንችለው ራሳችን፣ ድርጅታችን እና ተግባሮቻችን ለሥነሥርዓት ተገዢ ስናደርግ ነው። የነፃነት ታጋዮች ራሳቸውን ለሥነ ሥርዓት ያስገዙ መሆን ይኖርባቸዋል። አስተሳሰባችን ራሱ ሥነ ሥርዓት የያዘ ሊሆን ይገባዋል። እንደዚሁም ሁሉ ተግባሮቻችን በሥነሥርዓት የታነጹ ሊሆኑ ይገባል።
የንቅናቄዓችንን መዋቅር በመላው አገራችን ከዘረጋን፤ ራሳችንን፣ አስተሳሰቦቻችንና ተግባሮቻችን በሥነሥርዓት ከመራን፤ ቅንነት፣ ሀቀኝነትና ጽናት ከተላበስን ድላችን ቅርብ እና አስተማማኝ ነው። ለውጥን የሚናፍቅ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከላይ የተጠቀሱትን ተግባራት ይተግብር።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!