tirsdag 13. januar 2015

የኢትዮጵያ ምርጫ መቆመሪያ ተቋም ገመና

January 13,2014
በዳንኤል ተፈራ

10485535_718983234881727_4513979552309356105_n (1)
ያሳለፍነው ሳምንት በሕወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ተሰልተው፣ ታስቦባቸው ይፋ ከተደረጉና አሻንጉሊቱ ምርጫ ቦርድ እንዲፈጽመው በህወሃት ሰዎች ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጥቶት ገቢራዊ እንዳደረገው የሚጠረጠረው የፖለቲካ ጉዳይ ይፋ የተደረገበት ነበር፡፡ ይሄው ጉዳይ በአይረቤ ሰበብና በምክንያት አልባ ሁነት ግን ዳግም ከቤተ-መንግስት በወጣ ትዕዛዝ በሚመሰል መልኩ አንድነት እና መኢአድ ወደ ምርጫ ፍክክሩ እንዳይገቡ አይን ያወጣና የሰዎችን የስልጣን ብልግና ባጋለጠ መልኩ መግለጫ የሰጡበት ነው፡፡
እንደዚህ ዓመቱ ምርጫ ቦርዱ የተጋለጠበት ጊዜ አለ ብዬ አላምንም፡፡ ይሄው የምርጫ መቆመሪያ ተቋም እንደ ጫጩት ፍፁም ጠቅላላ ጉባዔ አድርገው የሚያውቁ፣ ቢሮም ሆነ ስራ አስፈፃሚ የሌላቸውን ተቃዋሚ ተብዬዎች በጉያው ሸጉጦ በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ላይ እያላገጠ መሆኑ ሳያንስ የገዥውን ፓርቲ ኃላፊነት የጐደለው ተግባር ተቋቁመው ለሃገራችን የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እየደከሙ ያሉ ፓርቲዎችን እየገፉ ያለበት አግባብ ተቋሙን ከምርጫ መቆመሪያ ማዕከልነት ባለፈ ፋይዳ የሌለው፣ በህወሃት/ኢህአዴግ ማንቁርቱ የታነቀና የራሱ ሳንባ የሌለው ምስኪን ተቋም እንደሆነ ለመገንዘብ ይቻላል፡፡
ይሄው የተጨመደደ ቦርድ ተብየ በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ ገለልተኛነቱ አጠራጣሪ ቢሆንም እንደ ሰሞኑ ገለልተኛ አለመሆኑን በይፋ ያረጋገጠበት ወቅት ያለ አይመስለኝም፡፡ የውስጥ አዋቂ ምንጮች እንደሚጠቁሙት ቦርዱ በዋናነት የሚመራው በፕ/ር መርጋ በቃና ሳይሆን በምክትልነት በተቀመጠው የትግራዩ ሰው ዶ/ር አዲሱ ገ/እግዚአብሄር ነው፡፡ ለዚህም ነው በኢህአዴጉ አፈ-ቀላጤ ፍና እና ሌላው ቀላጤ ኢቲቪ በኩል ፓርቲዎችን በህገ ወጥ መንገድ መገፋታቸውን እየገለፀ ያለው፡፡ ሰውየው የቦርዱን ህገ ወጥ ተግባር ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ የሚችል ሰው ነው፡፡ ዶ/ር አዲሱ የፓርቲዎችን የፋይናንስ ክፍፍል ቀመር አዘጋጅቶ ያቀረበ፤ በዚህ ቀመርም በፓርላማ መቀመጫና በክልል ም/ቤት መቀመጫ 55% እንዲይዝ ለማሳመን የጣረ የህወሃት የቁርጥ ቀን ልጅ ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም 55% ጠቅልሎ የሚወሰደው ኢህአዴግ ነው፡፡
ቦርዱ ገለልተኛ አይደለም ስንል እንዲሁ በግብታዊነት ሳይሆን ተጨባጭ መከራከሪያዎችን የማቅረብ አቅም ስላለን ነው፡፡ አንድ ወዳጄ የኢትዮጵያውን ምርጫ ቦርድ በማገዝ ከመቆሪያ ተቋምነት መገላገል እንደሚገባ ስነግረው ተስፉ በቆረጠ ስሜት ግን ደግሞ በምፀት ፈገግ ብሎ “ወዳጄ ቦርዱ እኮ ግንባሩን ከመሰረቱ ፓርቲዎች አምስተኛው ፓርቲ ነው፡፡ የሚያስፈልገው ቦርዱን ማገዝ ሳይሆን አፍርሶ እንደገና መስራት ነው፡፡ በታሪክ ከሚጠየቁ ተቋማት ግንባር ቀደሙ ነው፡፡” ነበር ያለኝ፡፡ እውነትም መፍረስ የሚገባው አይረቤ ተቋም ነው፤ ራሱን ነፃ ያላወጣና የምርጫ መቆመሪያ ተቋም እንደሆነ ግብሩ አረጋገጠ፡፡
አንድነት ፓርቲ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ኢ/ር ግዛቸው በፈቃዳቸው ስልጣናቸውን ከለቀቁ በኋላ አንድነት በመዋቅሩ በአመራርነት የማያውቃቸው ግለሰቦች ተሰባስበው ኢ/ር ግዛቸውን የተካውን አመራር ህግ የጣሰ ለማስመሰል ጥረት ጀመሩ፡፡ የቦርዱ የፖለቲካ ቁማርም ከዚህ ሁነት ይጀምራል፡፡ አንድነትን አስቀድሞ ከምርጫው ለማስቀረት እነዚህን ተራ ግለሰቦች “ጐሽ፣ ጐሽ” ማለት ጀመሩ፡፡ እነዚህ “አንድነት ነን፣ መርህ ይከበር” የሚሉ ጥቂት ግለሰቦች የተንኮል ፖለቲካው አድራሽ ፈርሶች እንጅ በራሳቸው ምንም አይደሉም፡፡ የእነዚህ አፍራሽ ግለሰቦች ያላቸው ብቃት የሚለካው ከኢትዮጵያዊ ጨዋነት ባፈነገጠ መልኩ ለመዋሸት የማይሳቀቁ፤ ተልዕኳቸውን ለመፈፀም አይናቸውን በጨው ያጠቡ የዘመናችን ባንዳዎች መሆናቸው ነው፡፡
ለዚህ ምሳሌ የሚሆነው የመቆመሪያው ተቋም ሳያፍር “አመራር” እያለ የሚጠራው የማነአብ አሰፋ የሚባል የትግራይ ተወላጅ ሲሆን ዕድሜው በሃያዎቹ መጀመሪያ የሚገኝ፣ በተግባሩ ስለሚያፍር በቆብና በጃኬት ራሱን ደብቆ የሚዞር ወጣት ነው፡፡ ይሄ ልጅ አንድነት ቤት ተቀጣሪ ሆኖ ለተወሰኑ ወራት የድርጅት ጉዳይ ተላላኪ ሆኖ ሰርቷል፡፡ አንገት ደፊና አይናፋር በመምሰል የተወነው ትወና አስደናቂ ነው፡፡ የኢህአዴግ ክትትል እንዳላስቀመጠውና ስራ መቀጠር እንኳን እንዳልቻለ እንባ እየተናነቀው ለመናገር የሚችለው ይሄ ወጣት ምርጫ ሲደርስ እንዲፈነዳ ህወሃት አቀባብሎ ያስቀመጠው ፈንጂ እንደሆነ ያወቅነው ቦርዱ “አመራር” እያለ ቢሮው ጐልቶት ስናገኘው ነው፡፡ ወደ ነጥቡ ስንመለስ እነዚህ “አንድነት ነን” የሚሉ በተግባር ግን የአንድነት ወገን ያልሆኑ ስብስቦች ም/ቤቱ በደንቡ መሰረት የተካውን አመራር “ህገ-ወጥ ነው” በማለታቸው ብቻ የምርጫ መቆመሪያው ተቋም በችኮላ አንድ ደብዳቤ ለፓርቲው ፃፈ፡፡ ይሄ የመጀመሪያው ደብዳቤ ኢ/ር ግዛቸውን ፕሬዝዳንት አድርጐ የመረጠውን ጉባኤ ዕውቅና በመንፈግ ዶ/ር ነጋሶን እንደሚያውቅ የሚጠቅስ ነው፡፡ ቦርዱ በችኮላ በየዋህነት የፃፈው ደብዳቤ ለቁማሩ በጆከርነት የሚያገለግሉ ግለሰቦችን ከጨዋታ ውጭ የሚያደርግበት መሆኑን ሲረዳ ምናልባትም አለቃቸው ህወሃት /ኢህአዴግ ለአንድነት ቦርድ የፃፈውን ዝርዝር ደብዳቤ ሲመለከት ለሴራ ፖለቲካ እንደማይመች ሲረዳ በአስቸኳይ ቀይር ብሎት ይመስለኛል፡- “እሱን ደብዳቤ ተውት” ከሚል መልዕክት ጋር ሌላ 3 ነጥቦችን የያዘ ደብዳቤ ላከ፡፡
የመጀመሪያውን ደብዳቤ ተውት ያለበት ምክንያት ለአፍራሽ ተልዕኮ የተዘጋጁ ገልቱ ግለሰቦች ከጨዋታ ውጭ ስለሚሆኑ ነው፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ግለሰቦች በዶ/ር ነጋሶ የአመራር ዘመን አይታወቁም ወይም የሉም ነበርና፡፡ ባለ ሦስቱ ነጥብ ደብዳቤ ሲመጣ ግን አንድነት የፖለቲካ ዕደንድምታውን በጥንቃቄ ገምግሟል፡፡ ምነው ቢሉ ይሄ ከቦርዱ በስተጀርባ የሚደንስ አካል እንዳለ በመረጋገጡ ነው፡፡ ዳንሰኞቹ ምርጫን ለማስመሰያና ማወናበጃ እንጅ በትክክል ሊጠቀሙበት አይፈልጉም፡፡
የደብዳቤው ሦስት ነጥቦች የሚከተሉት ነበሩ አንደኛው ም/ቤቱ የጠቅላላ ጉባኤ ውክልና እንዳለውና ም/ቤቱ ፕሬዘዳንት መምረጥ እንደሚችል አብራሩ፤ ሁለተኛው የጠ/ጉባኤ ሪፖርት በጊዜ አስገቡና የመጨረሻው የጠቅላላ ጉባኤ የኮረም ቁጥር ግለጹልን የሚል ነበር፡፡ በጣም ቀላልና ተራ ጥያቄ የሚመስል ነበር፡፡ አንድነት በፍጥነት ምላሽ ሰጠ፡፡ የመቆመሪያው ተቋምም የሰጠነውን ምላሽ “በቅንነት” እንደተቀበለው ገልጾ ነገር ግን የጠ/ጉባኤ ቁጥር በደንቡ እንድናካትት የሚጠይቅ ደብዳቤ ፃፈ፡፡ በቅንነት የምትለውን ግን በቅንነት አልተመለከትነውም፡፡ ጉባኤ በፍጥነት መጠራት እንዳለበትና ምርጫ ቦርዱ የጠየቀውን አሟልተን በሙሉ ልብ ወደ ምርጫ መግባት እንደሚገባ በመታመኑ በሳምንት ጊዜ ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ የምርጫ ቦርድ ተወካይ ባለበት በስኬት ተጠናቀቀ፡፡
አንድነትም ገዥዎች ባዳፈኑት የፖለቲካ ምህዳር እና ልፍስፍሱ ቦርድ ቢኖርም ህዝቡን አንቀሳቅሽ በ2007 ዓ.ም የአምባገነኑ ስርዓት ፍፃሜ ይሆናል በሚል ፅኑ እምነት ሙሉ ለሙሉ በስራ ተጠመደ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜም የህዝብ ታዛቢዎችን ምርጫ በመላ ሀገሪቱ ያሉ ቢሮዎቹን በመዝጋት በንቃት ተከታተለ አጋለጠ፡፡ ህዝቡ የምርጫ ካርድ የሚወስድበትንና በካርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ አሸናፊ የሚሆንበትን ስትራቴጂ መንደፍንና ሕዝባዊ ንቅናቄ እንደሚያስፈልግ ይፋ ማድረጉ ተከትሎ የ40 እና 50 ዓመት የመግዛት ህልም ያላቸው “ነፃ አውጭዎች” መንደር ጫጫታና ጭንቀት ፈጠረ፡፡
ይህንን ጭንቀት ለማርገብ አንድነትን ከምርጫ ጫወታ ማስወጣት እንደሚገባ ታመነበት፡፡ ለዚህ ማስፈፀሚያ የመቆመሪያው ተቋም አለ፡፡ በጠቅላላ ጉባኤው ተወካዩን የላከው ቦርዱ ሌላ ታሪካዊ ስህተት ለመስራት ደፈረ፡፡ ከቦርዱ በስተጀርባ ያሉ ዳንሰኞች ማንቁርቱን ስላነቁት ምርጫ አልነበረውም፡፡ ይሄ ተራ ጨዋታ በፋና እና ኢቲቪ ታጅቦ ለህዝብ ቀረ፡፡ ድራማው “የውስጥ ችግሮቻቸውን ካልፈቱ ወደ ምርጫ አይገቡም” የሚል ነው፡፡ የውስጥ ችግር ከማን ጋር? እንዴት? መልስ የላቸውም፡፡ ኢ/ር ግዛቸው በፈቃዳቸው ለቀው ወደ ግል ጉዳያቸው ገብተዋል፡፡ ታዲያ እነዚህ አመራር ተብየዎች እነማን ናቸው? እነዚህ የአንድነት አመራር እንዲደራደራቸውና ችግሩን እንዲፈታ የተጠየቁት ግለሰቦች በፓርቲው የአመራር መዋቅር የማይታወቁ፤ ከየመንገዱ ተለቃቅመው የመጡ ተራ ሰዎች ናቸው፡፡
ህወሃት/ኢህአዴግ በቦርዱ በኩል ይህንን ተራ ድራማ እየሰራ ያለው አንድነት ወደ ምርጫ እንዳይገባ ለመከልከል የወሰነው የፖለቲካ ውሳኔ ስጋ ለማልበስ ነው፡፡ የእርኩም ስጋ፡፡ ሁሉም በሰፈረው ቁና የሚሰፈርበት ቀን እንደሚመጣ ቅንጣት አልጠራጠርም፡፡ እየተካሄደ ያለው ሰላማዊ ትግል ከዚህ ዓይነት ተራ ድራማ በላይም ነው፡፡ ትግሉ የነፃነት የመውጣትና ተደፍቆ የመኖር ነው፡፡ ወደ ምርጫ እንገባለን ስንላቸው በዚህ ደረጃ ተርበትብተዋል፡፡ ምርጫ ቦርድም ያለውድድር ለኢህአዴግ ተጨማሪ የአገዛዝ ዘመን ለመስጠት ዝግጅቱን የጨረሰ ይመስላል፡፡ ይሄ የስርዓቱን የውድቀት ፖለቲካ የሚያሳይ ነው፡፡ የዚች ሀገር ትግል የቦርድ ወይም የሌላ ትግል አይደለም፡፡ ትግሉ በሕዝቡ እጅ ላይ የወደቀበት ታሪካዊ ወቅት ነው፡፡ ታሪካዊ ጊዜ ዴሞክራሲን እናሰፍናለን የሚሉ ሰዎች በግብራቸው ያፈሩበት ታሪክ፡፡ ይህንን በአደባባይ ቆመን የምንናገርበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፡፡
2007 ለለውጥ!!!

torsdag 1. januar 2015

ቀኑ ሲቃረብ መውጫው ይጠባል!

ኢትዮጵያ ሀገራችን በታሪኳ ከአስከፊ የፈተና አረንቋ ውስጥ ተገፍታ የገባችበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ ዜጎችዋ ከፋሽስት ኢጣልያ በከፋ ሁኔታ ይህ ቀረሽ የማይባል የመከራ መአት የወረደባቸውና እየወረ ደባ ቸው የሚገኝበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመን ወያኔ ብቻ ነው፡፡ እስር ቤቶች ሞልተው ተጨማሪ እስር ቤቶች መገ ንባት ከልማት ተቆጥሮ የሚፎከርበት ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የሀገሪቱ ብሄራዊ ባንክ ንብረት የሆ ነው ወርቅ በባሌስትራ ለውጦ እስከ መዝረፍ የደረሰ በጠራራ ፀሀይ የህ ዝብና የሀገር ሀብት ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ በጥቂቶች የሚዘረፍበት ዘመን ቢኖር የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የጅምላ እስር፤ የጅምላ ግድያ፤ የጅምላ ስደትና መፈናቀል፤ ይበልጡንም በታሪካችን ታይቶ በማያውቅ መልኩ ለሞት፤ ለእስር፤ ለመፈናቀልና ለስደ ት ምክንያቱ የተገኘንበት ዘውግ የሆነበት ዘረኛ ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡

ባጠቃላይ ላለፉት 23 አመታት ወያኔ ማድረግ የሚችለውን አስከፊ ነገር ሁሉ በሀገርና በህዝብ ላይ ሲፈፅም ቆይቷል፡፡ ዛሬ ከ23 አመ ታት በዃላ ሀገራችንና ህዝባችን ያልተዘፈቁበት የችግር ማጥ፤ ያልደረሰ የሀብትና የሰብአዊ ውድመት፤ ያልተፈፀመ የግፍና የሰቆቃ አይነት የለም፡፡ ወያኔ ይህን ሁሉ ሲፈፅም መሳሪያ አድርጎ ከተጠቀመባቸው ተቋማት ውስጥ ዋነኛዎቹ የመከላከያ፤ ፍርድ ቤትና የፖሊስና የደህንነት መሆናቸው ጥያቄ የለውም፡፡ የእነዚህ ተቋማት አባላት ከወያኔ ጥቃት ሰለባ ከመሆን ባይተርፉም የዚህን ወንጀለኛና ዘረኛ ቡድን እድሜ በአንድ ቀን በመጨመሩ ስራ ላይ ከፍተኛውን ድርሻ እንደያዙ ዛሬም መገኘታቸው አሌ የማይባል እውነት ነው፡፡ይህ ሲባል ግን በሀገርና በህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ክህደት፤ ግፍና ሰቆቃ የሚያማቸው፤ መከራው መረራቸው፤ ብሶቱ ብሶታቸው የሆኑ አባላት የሉም ማለት እንዳልሆነ፤ ይልቁንም አብዛኛዎቹ የዚህ ስሌት ተካፋይ ስለመሆናቸው የሚጠራጠር የለም፡፡
ነገር ግን ከህዝብ አብራክ በወጡና ልጆቹን ሳይመግብ በከፈለው ታክስ በተደራጀ የመከላከያ፤ የፖሊስና የደህንነት ተቋማት ውስጥ የምትገኙ አብዛኛውና የግፉ ቀማሽ የሆናችሁ አባላት ዛሬ የምትገኙበት ሁኔታ እንደ አለፉት 23 አመታት በማወቅም ሆነ ባለማወቅ፤ ከዛሬ ነገ የተሻለን ነገር ተስፋ በማድረግ፤ በግርግሩ ፍርፋሪ ሊወድቅልኝ ይችላል ከሚል ራስ ወዳድነት…… ወዘተ በመሳሰሉ በርካታ ምክንያቶች ለፍትህ፤ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ ብሎም ለኢትዮጵያችን ቀጣይ ህልውና በሚደረጉ ህዝባዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በመቆም ብሎም የጥቂት ዘረ ኛች ስልጣንና ምቾት እድሜ ለማራዘም የተጓዛችሁበት መንገድ ብዙም ማስኬድ ከማያስችልበት፤ ይልቁንም ዛሬ ከሁለት መንታ መንገድ የ ደረሳችሁበትና ቆም ብሎም ማየትና ማገናዘብን ከሚጠይቅ ወቅት ላይ ትገኛላችሁ፡፡ አንዱ በዘረኝነት በትር እየተወቀጡ የወያኔ ሎሌ ሆኖ መቀጠል፤ ሌላው ከህዝብ አብራክ የተገኛችሁ ናችሁና ከህዝብ ወገን ተቀላቅሎ ሀገርን፤ ወገንንና ራስን ነፃ ለማውጣት መነሳት..
ለመከላከያ ሰራዊት፦ ላለፉት 23 አመታት ከጠመንጃ ተሸካሚነት ላለፈ ለማይፈልጉህ፤ ለአንተነትህ መለኪያው እውቀትህ፤ ችሎታ ህና አገልግሎትህ ሳይሆን የተገኘህበት ዘውግ መስፈሪያህ ለሆነበት ዘረኛ ስርአት፤ መቀየሪያ መለያ ልብስ ተነፍጎህ ቀዳዳ እየጣፍክ የልጆችህን የረሀብ ልቅሶ እያዳመጥክ በአንተ ትከሻ በዘረፉት ሀብት የገነቧቸውን ህንፃዎች ጠባቂ ላደረጉህ፤ ፍትህ ነፃነት ሲል በተራበ አንጀታቸውና በደ ከመ ድምፃቸው በጠየቁ ወገኖችህ ላይ ይህ ቀረ የማይባል ግፍ ሲያ ስፈፅምህ ለቆየው የወያኔ ዘረኛ ቡድን ዛሬም ተገቢውን ምላሽ የመስጠት እድሉ አለህ፡፡አልረፈደምና ተጠቀምበት!!!
የፖሊስ ሰራዊት አባላት፤- ፍትህ ላሉ ጥይትን፤ ነፃነት ላሉ የጭካኔ በትርን፤ ሀገሬን ላሉ ከጨለማ ዘብጥያ መወርወርን.. ዋነኛ ተግባርህ በሆነበት በዚህ ዘረኛና በወንጀል የተጨማለቀ ስርአት ውስጥ የቆየህበት ያለፉት 23 አመታት ለአንተም፤ ለቤተሰብህም፤ ለተገኘህበት ህብረ ተሰብ ሆነ ለሀገርህ የፈየደው አንዳች ነገር ያለመኖሩን ይበልጡኑ ከእሳት ወደ እረመጥ ከሆነው የወያኔ ጉዞ ራስህን አውጥተህ ከህዝባዊው ወገን የምትቀላቀልበት የመጨረሻው ሰአት መሆኑን ተገንዝበህ ምርጫህን ከወገንህ አድርግ፡፡ ለአንተም አልረፈደም!!
የደህንነት አባላት፦ ለሀገር ደህንነት ለህዝብ ሰላም ሲባል በህዝብ ሀብት በተደራጀ ተቋም ተጠቅመህ በሀገርህ ላይ ክህደትን፤ በወገ ንህ ላይ ግፍና ሰቆቃን ስትፈፅም መቆየትህ ከወንጀሎች ሁል የከፋ ወንጀል መሆኑን ተገንዝበህ ለፍትህ ለነ ፃነትና ለዲሞክራሲ ሲሉ በተነሱ ወገኖችህ ላይ ስትሰነዝር የቆየኸውን በትር በፍትህ በነፃነትና በዲሞክራሲ ላይ በቆሙት ዘ ረኛ አዛዦችህ ላይ የማሻው ጊዜ አሁን ነው፡፡ ስለ ዚህም ከህዝባዊው ወገን ተቀላቅለህ ህዝባዊ ወገንተኝነትህን የምታሳይበት ብሎም የበደልከውን የምትክስበት ጊዜውም እድሉ አለህና ተጠ ቀምበት፡፡ላንተም አልረፈደም!!
በመጨረሻም ልጇን የምትጠላ እናት፤ ወገኑን የሚገፋ ህዝብ፤ ዜጎቹን የማይቀበል ሀገር የለምና ይህን በአስከፊነቱ ወደር የማይገኝለት የወያኔ ዘረኛ ስርአት ደግፎ ማቆየት ከማይቻልበት ይበልጡንም እንደ ትሪፖሊና ኢያሪኮ የግፈኞች ግንብ በህዝባዊ ሀይል ከሚገረሰስበት ከ መጨረሻዋ ደቂቃ ከመደረሱ በፊት ከእናታችሁ እቅፍ ከወገናችሁ መሀል ግቡ!! ተቀላቀሉ!! ቀኑ ሲቃረብ መውጫው ይጠባልና ጊዜ ሳታጠ ፉ ፈር ቀዳጅ ወንድሞቻችሁን መከተል ብልህነት ነው እንላለን!!!
የኢያሪኮም የጋዳፊም ግንብ ተንዷል፤ የወያኔም ይናዳል!!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!