lørdag 29. mars 2014

ኑ! እንዋቀስ፤ ኢህአዴግንም እናፍርሰው! (ተመስገን ደሳለኝ)

March 29, 2014
(ይህ “ኑ! እንዋቀስ” የሚለው ስር ነቀል የለውጥ ጥሪ ቀጥታ የሚያነጣጥረው በኢህአዴግ አባላት ላይ ብቻ ነው፤ አመራሩን በፍፁም አይመለከትም)
ኢህአዴግ ራሱ በይፋ ሲናገር እንደተደመጠው፣ በአሁኑ ጊዜ የአባላቱ ቁጥር ወደ ሰባት ሚሊዮን ገደማ ደርሷል፡፡ ይህም የአገሪቱ ቁጥር አንድ ግዙፍ የፖለቲካ ፓርቲ ያደርገዋል፡፡ በርግጥ ግዙፍ እንጂ ጠንካራ እንዳላልኩ ልብ ይሏል፡፡ ምክንያቱም ጥንካሬ የሚለካው በአባላት ቁጥር ሳይሆን በድርጅት ፍቅር፣ በዓላማ ፅናትና በሚሰጡት ልባዊ አበርክቶ ነው፡፡Journalist Temasegan Dasaleg
እንዲህ ያለ አቋመ-ብርቱነት ደግሞ ድሮ በያ ትውልድ ጊዜ ቀርቷል፡፡ በዘመነ-ኢህአዴግ የተንሰራፋው ጥቅመኝነት (በእነርሱ ቋንቋ ኪራይ ሰብሳቢነት) ብቻ ነው፡፡ ለዚህም በደቡባዊቷ አዋሳ ከተማ ስድስተኛው የድርጅቱ ጉባኤ በተካሄደበት ወቅት፣ አቶ በረከት ስምኦን በብስጭት እየተትከነከነ በደፈናው ለጥቅም ድርጅቱን የተቀላቀሉ አባላት በርካታ መሆናቸውን አምኖ በአደባባይ መናገሩ አስረጂ ሊሆነን ይችላል፡፡ ይህን ንግግሩንም አፍታተን ስናብራራው እንደሚከተለው ሆኖ እናገኘዋለን፡- የግንባሩ አባላት ቁጥር ሰባት ሚሊዮን ገደማ የደረሰው በጥቅም በመደለል፣ በአንድ ለአምስት የጥርነፋ መዋቅር በፍርሃት ተጠፍንጎ በመያዙና በመሳሰሉት ነው (መቼስ አቶ በረከት ከድርጅቱ ጉምቱ መሪዎቹ አንዱ ነውና ዘርዝሮ እንዲያስረዳን አይጠበቅበትም)
የሆነው ሆኖ አባላቱ እንዲህ የመብዛታቸው ምስጢር የድርጅቱ አምባ-ገነንነት ባህሪይ መገለጫ እንጂ አመላይ አጀንዳ አሊያም ምትሀታዊ ችሎታ እንዳለው የሚያሳይ አይደለም፡፡ ይህ የትኛውም መሰል ሥርዓት ከተጠናወተው ሁሉንም ከመቆጣጠርና መጠቅለል (Totalitarianism) አስተሳሰብ የሚሰርፅ ማኪያቬሊያዊ አስተምህሮ ነው፡፡ የሆነው ሆኖ ‹‹አምባገነኖች የአንድ እናት መንትያ ልጆች ናቸው›› እንዲሉ፤ በ‹‹ቆራጡ መሪ›› ዘመነ-መንግስትም በጊዜው ከነበረው የሀገሪቱ ሕዝብ ቁጥር አኳያ መሳ-ለመሳ ሊባል በሚያስደፍር ሁኔታ ሳር ቅጠሉ ሁሉ ሰማያዊ ካኪ ለባሽ የኢሠፓ አባል ሆኖ ነበር፡፡ ግና፣ ያ ካኪ ለባሽ ሕዝብ፣ የልቡን በልቡ ይዞ ‹‹ቪቫ መንጌ!›› እያለ አሳስቆ በስተመጨረሻ ጉድ እንደሰራው ሁሉ፤ ‹‹ይህ የህዝብ ማዕበል…›› ተብሎ በአቶ መለስ ዜናዊ የተሞካሸው የ97ቱ የቅዳሜው መሬት አንቀጥቅጥ የሰልፍ ትዕይንትም፣ በድጋፍ ሳይሆን በግዳጅ የሰመረ መሆኑን ለማየት፤ አይቶም ለመመስከር ከሃያ አራት ሰአት ጊዜ በላይ አልወሰደብንም፡፡ እንዴት? ቢሉ በማግስቱ (ሚያዚያ 30) ለተቃውሞ ከወጣው ሕዝብ የቅዳሜዎቹም በብዛት መሳተፋቸውን በራሳቸው አንደበት ‹‹ትላንት ለቲሸርት፤ ዛሬ ለነፃነት!›› በሚል ሕብረ-ዝማሬ ከአደባባዩም አልፎ ከተማዋን በሚያናውፅ የለውጥ ጩኸት የመሰከሩበት ‹‹ፖለቲካ›› መቼም ቢሆን አይዘነጋምና፡፡
እንግዲህ ይህ ሁሉ ታሪካዊ ሀቅ የሚገልፅልን አንድ ታላቅ እውነት-በጥቅም እየደለሉ አባልን ማብዛት በክፉ ቀን የማይታደግ መሆኑን ነው፡፡ ጥቅመኝነት ግፋ ቢል የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ‹‹ፀበል›› ያስጠምቅ፣ ‹ኢህአዴግ ጌታ ነው!›ን ያስፎክር ያሸልል ይሆናል እንጂ የኢትዮጵያን ትንሳኤ መሻትን አያስቀይርም፡፡ ነብር ዥንጉርጉርነቱን እንደማይለውጠው ሁሉ የኢህአዴግ አባላትም ምንም ቢሆን ምን፣ እንደሌላው ሕዝብ የሀገር አንድነት የሚያሳስባቸው፣ ብሔራዊ ውርደት (ረሀብተኝነት) በቁጭት የሚያንገበግባቸው፣ ከዘውግ ልዩነት የሕዝብ ለሕዝብ መተማመንና አንድነታዊ ጥንካሬው የሚበልጥባቸው፣ የኃይማኖት ነፃነት የሚያስተቃቅፋቸው… ናቸው ብዬ አምናለሁ፡፡ ምክንያቱም ጥቅመኝነት የእጦትን ክፍተት ለመሙላት ለጊዜው ያሰግዳል እንጂ ክብርንና ማንነትን አስሽጦ በባርነት ቀንበር አያሳድርም-በተለይም ዥንጉርጉርነቱን ጠንቅቆ ለሚያውቀው ኩሩ-ሀበሻ!
ደግሞስ ምን ያህሉ አባል ነው፣ የድርጅቱን መታወቂያ በመያዙ ብቻ የረባ ጥቅም ያገኘው? በግላጭ እንደሚታየው በግል ጥቅምም ሆነ በተጭበረበረው የዘውግ ፖለቲካ ሳቢያ ኢህአዴግን የተቀላቀሉ የአብዛኞቹ አባላት የኑሮ ደረጃ ዛሬም እንደ ብዙሃኑ የኢትዮጵያ ህዝብ ከችግር የመቆራመድ አስከፊ ሕይወት አልተላቀቀም፡፡ ፓርቲውን መታከካቸውም በማይጨበጥና በማይታይ እንቅልፍ የለሽ ሕልም አናውዞ ይበልጥ ደቁሷቸዋል እንጂ በቀን ሶስቴ መመገብ እንኳ አላስቻላቸውም፡፡ ሌላው ቀርቶ የድርጅት አባልነታቸው እንደተርታው ሕዝብ በአድሎአዊ አሰራር መማረርን እንዳላስቀረላቸው በርግጠኝነት መመስከር ይቻላል፡፡
ይህ አይነቱም እርግጠኝነት ነው ‹ኑ! እንወቃቀስ (እንነጋገር)፤ እንተማመንምና ሀገርና ትውልድ እየገደለ ያለውን ፓርቲያችሁን አብረን ተጋግዘን እናፍርሰው› የሚል የማንቂያ ደውል ላሰማችሁ ገፊ-ምክንያት የሆነኝ፡፡ እናም ድርጅታችሁን ትመረምሩ ዘንድ ወደድኩ፡-
ድርጅታችሁ ሥልጣን ላይ ተፈናጥጦ ባሳለፋቸው ሁለት አስርታት የተጓዘበትን መንገድ በአስተውሎት ብትመረምሩ፤ በእርግጠኝነት እንደ ግዙፍ ዐለት ካገጠጡ ሀገራዊ ውድመቶች እና ከበባድ ኪሳራዎች ጋር መፋጠጣችሁ አይቀሬ ነው፡፡
ይህም ሆኖ በቅድሚያ በተልካሻ ፕሮፓጋንዳ ያሰለቸንን የብሔር ጉዳይ (የተወሰኑ ሰዎችን አማልሎ አባል ለማድረግ አስተዋፆ እንዳለው ባይካድም) ወደጎን ብለን፤ የትኛውም ብሔረሰብ ባህላዊ እሴቶቹን ማክበር፣ በአፍ መፍቻ ቋንቋው መጠቀም… የፖለቲካ ፓርቲ በችሮታ የሚሰጠው ሳይሆን፣ የማንም ተፈጥሮአዊ መብት መሆኑን ማስረገጥ አስፈላጊ ይመስለኛል፡፡ ይህ ማለት ግን የድርጅታችሁ ሀቲት፡- ‹አንዱ በሌላው እድሜውን ሙሉ ሲጨቆን እንደኖረ፤ ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ የተለየ እንደሆነ፤ ከብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማችን ይልቅ የክልሉን እንዲያስቀድም መቀስቀስና መስበክን የብሔር ብሔረሰብ መብትን ማክበር ነው› የሚለውን አምኖ መቀበል አይደለም፡፡ በግልባጩ ስርዓቱ እንዲህ አይነት ጉዳዮችን ሰማይ ጥግ አጉኖ፣ ሕዝብን ከፋፍሎና በጥርጣሬ (በጎሪጥ) ወደሚተያይበት ጠርዝ ገፍቶ፣ የሥልጣን ዕድሜውን ያራዘመበት ሁለት አስርታትን ያሳለፈ ስልቱ መሆኑን መረዳት አይሳናችሁም ብዬ አስባለሁ፡፡
ሌላ ሌላውን ትተን እንኳ የኢህአዴግን አመሰራረት ብንመለከት ግንባሩን ከፈጠሩት አራቱ ድርጅቶች መካከል ከሞላ ጎደል ህወሓት እና ኢህዴን/ብአዴንን እንደ ፖለቲካ ድርጅት መውሰድ ይቻል ይሆናል እንጂ፤ ኦህዴድና ደኢህዴን፣ በህወሓት ‹‹አባ መላ››ዎች እንደ የፋብሪካ ሳሙና በሚፈለጉበት መጠንና ቅርፅ ተጠፍጥፈው ከተሰሩ በኋላ በኦሮሞና በደቡብ ኢትዮጵያ ተወላጆች ላይ እንደ አለቅት የተጣበቁ የመሆናቸውን ምስጢር እነርሱም ራሳቸው የሚክዱት አይመስለኝም (ምናልባት በሽግግሩ የመጀመሪያ ዓመት ላይ እንደአስተዋልነው ከኦህዴድ ይልቅ፣ ኦነግ ኦሮሚኛ ተናጋሪዎችን ወክሎ ቢቀጥል ኖሮ ይህ ጉዳይ በዚህ አውድ ላይነሳ ይችል ነበር፡፡ የሆነው ግን ተቃራኒው ነው፤ የራሱ የፖለቲካ ቁመናና ራዕይ የነበረው በኃይል ተገፍቶ፤ በምትኩ በሌሎች እስትንፋስ ህልው ሆኖ
‹‹የሚያስተዳድረው››ን ሕዝብና ራሱንም ጭምር ቀን ከሌት ‹‹ከብሔር ጭቆና ነፃ አወጣናችሁ›› ስለሚሉት ሞግዚቶቹ ገድል መተረክን ‹‹ፖለቲከኛነት›› አድርጎ የወሰደው ኦህዴድን ያነገሰ ነውና)
በነገራችን ላይ የፖለቲካ ፓርቲን እንደ ፋብሪካ ምርት ጣጣ-ፈንጣጣው ተጠናቅቆለት ሲያበቃ የመጫኑ አሰራር በሁለቱ ክልሎች ብቻ ተገድቦ የቀረ አይደለም፤ አጋር ፓርቲዎችንም ይመለከታል፡፡ ከአፋር እስከ ጋምቤላ እና ቤንሻንጉል፤ ከሀረር እስከ ሶማሌ ሲተገበር በትዝብት የተመለከትነው ጉዳይ ነው፡፡ መቼም ገና ከስር መሰረቱ ‹‹እኛ እናውቅልሀለን!›› በሚሉ ‹‹የፖለቲካ ሞግዚቶች›› የተፈጠረ ድርጅት በምደባ ቦታውን ያገኙ የአመራር አባላቱን በቅምጥል ኑሮ ከማንፈላሰስ በዘለለ፣ ‹‹እወክለዋለሁ›› ለሚለው ሕብረተሰብ ትርጉም ያለው ስራ ይሰራል ተብሎ የሚታሰብ አይደለምና ‹በኦሮሚያ ሙስና እንደሰላምታ እጅ መጨባበጥ ተዘውታሪና ተራ ነገር ነው›፣ ‹በአፋር ባጀት መቀለጃ ሆኗል›፣ ‹በሐረር ቤተሰባዊ ኢምፓየር ተገንብቷል›፣ ‹ቤንሻንጉል በድህነት ማቀቀ›፣ ‹ሶማሌ ክልል የአስተዳዳሪው አብዲ ርስተ-ጉልት ሆነ› ጂኒ ቁልቋል እያሉ ሮሮዎችን ማሰማት ለውጥ አያመጣም፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ህወሓትን እንደ ‹‹ግል አዳኝ›› በመቀበላቸው ብቻ ‹‹የአስተዳዳሪነት›› ካባ የተደረበላቸው ምስኪን የአመራር አባላት በቀላል ጉዳይ ላይ እንኳ የመወሰን ሥልጣን የላቸውምና ነው፡፡
ይህ እንግዲህ በቀጥታ ከኢህአዴግ ስነ-ተፈጥሮ ጋር የሚጋመድ ችግር ነው፡፡ ሆኖም የመንግስት ሥልጣን መዘውር ከጨበጠ በኋላ የጨፈለቃቸውን የዴሞክራሲና ሰብዓዊ መብቶች ተከትሎ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የደረሱ የአያሌ ሰላማዊ ዜጐች ግድያ፣ እመቃ፣ ከስራና ቤት ንብረት መፈናቀል፣ ስደትን… አንድ በአንድ ጠቅሰን ለማውገዝ ብንሞክር ሰማይ-ብራና፣ ቀይ ባህር-ቀለም ሆነው ካልተመቻቹልን በቀር የሚደፈር አይመስለኝም፡፡ በርግጥ በኢህአዴግ ውስጥ ታላቅና ታናሽ ንጉሠ-ነገሥት የሆኑት ህወሓትና ብአዴን ብረት ነክሰው፣ ሳንጃ ወድረው በትጥቅ ትግል ያለፉ ከመሆናቸው አኳያ ለየትኛውም አይነት ቅራኔም ሆነ ልዩነት ከመግደልና መጋደል ውጪ ያለ ሌላ ሰላማዊ አማራጭ ላይዋጥላቸው እንደሚችል መዘንጋት የለበትም፡፡ ኦነግ ከሽግግር መንግስቱ ከተገፋበት ጊዜ አንስቶ በኦሮሚያ፣ በአዋሳ፣ በሶማሌ… ግፉአን ያለቁበትን፤ እንዲሁም በድህረ-ምርጫ 97 የታየው የጎዳና ላይ ጭፍጨፋ ይህንኑ ሀቅ ያስረግጣሉ፡፡
ኩነቱም ግንባሩ በመጣበት አይነት የነፍጥ የበላይነት ያለፉት ሶቪየት ህብረት፣ ቻይና፣ ቬትናም፣ ኩባ፣ ኤርትራ ባሉ ሀገራት ከታየው የሕዝቦች እልቂት፣ የተቀናቃኝ ድምፆች መታፈን፣ የጋዜጠኞች መጨፍለቅ… ጋር ቀጥታ ዝምድና አለው፡፡ እነዚህ ሀገራትንም ሆነ ኢህአዴግን የተለየ ሃሳብ ለማስተናገድ ትዕግስቱም ፍላጎቱም እንዳይኖራቸው ያደረገው ይህ ከውልደታቸው ጀምሮ ከደም-አጥንታቸው ጋር የተዋሃደው ተፈጥሮአቸው ይመስለኛል፡፡
በአናቱም ኢህአዴግ ከአባላቱ ይልቅ የአመራሩ ‹‹ፓርቲ›› ብቻ ስለመሆኑ ለመረዳት የውስጥ አሰራሩን መፈትሽ የተሻለ ይሆናል፤ እናንተም በቅርበት እንደምታውቁት በድርጅቱ ያልተፃፈ ሕግ ከላይ ወደታች የሚወርድ መመሪያን ትክክል ሆነም አልሆነ ‹‹ለምን?›› ብሎ መጠየቅ የሚያስቀስፍ ሀጢያት ነው፡፡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለመወያየት መሻት፣ ጥያቄ ማቅረብ፣ ሃሳብን መቃወም፣ ስህተቶችን ማጋለጥ… አሳድዶ በድንጋይ የሚያስወግር አሊያም ከሀገር ሀገር የሚያሰድድ ታላቅ ጥፋት ተደርጎ ይቆጠራል፡፡
ይህ ሁናቴም ነው የአስተዳደር ድክመቶቹንም ሆነ አውዳሚ ጉድለቶቹን በፍጹም ለሕዝብ እንዳይደርሱ ገትሮ መያዝን የማይዘናጋበት ዋነኛ መንግስታዊ ስራ ያደረገው (የነፃው ፕሬስ ጋዜጠኞችን እና የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን በውሃ ቀጠነ ወደ እስር ቤት ሲያግዝ መክረሙን ልብ ይሏል) በጥቅሉ ድርጅቱ ለአመራሮቹ ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በተደረገባቸው ዘመናዊ “V8” መኪናዎች እንዲምነሸነሹ እና በቢሊዮን የሚቆጠር የሀገር ሀብት እንዲዘርፉ የሚያስችል ስልጣን ከማጎናፀፉ ባለፈ፤ እናንተ (ብዙሀኑ አባላት) ያተረፋችሁት ምንድር ነው? በአነስተኛና ጥቃቅን ከመደራጀት፣ ‹‹ኮብል-ስቶን›› ፈልጦ ከመደርደር የዘለለስ ማን ምን ሊጠቅስ ይችላል? እስቲ! የተራቆተችና በድህነት ወጀብ የተንገላታች ሀገራችሁን በዓይነ-ልቦናችሁ ለማስተዋል ሞክሩ፡፡
ያን ጊዜም ገና ጀንበር ስታዘቀዝቅ ስጋቸውን ለመቸርቸር ጎዳናዎችን የሚያጥለቀልቁ እምቦቀቅላ እህቶቻችን፣ ‹‹ማምሻም ዕድሜ ነው›› እንዲሉ የመፅዋች ዓይን እየገረፋቸው በልመና ቁራሽ ሕይወታቸውን የሚውተረተሩ አዛውንትና ህፃናት፣ በየጎዳናው በየሰፈሩ ሲንገላወዱ የሚውሉ ስራ-አጥ ወጣቶች፣ በቀን አንዴ ለመመገብ ላይ ታች የሚማስኑ ለፍቶ አዳሪዎች… ምድሪቷን እንዳጨናነቋት ይገለፅላችኋል፡፡ የዚህ ሁሉ መንስኤም የፈጣሪ ቁጣ ሳይሆን ፅንፈኛው ድርጅታችሁ በሚከተለው በተግባር ያልተፈተነ (የሀገሪቱን ተጨባጭ እውነት ያላገናዘበ) ርዕዮተ-ዓለም፣ ፖሊሲ፣ አድሎአዊ አሰራር፣ ሙስና እና ለኃላፊነት የማይመጥኑ ‹‹አስፈፃሚዎች›› ችግር ስለመሆኑ ለአፍታም ቢሆን ጥርጣሬ አይግባችሁ፡፡
እናም ጉዳዩ የሀገር ነውና በግልፅ እንወቃቀስ (እንነጋገር)፤ ስለምንድነው በአባልነት በምታገለግሉት ኢህአዴግ የሚመራው መንግስት ‹ዛሬም በስኬት ጎዳና እየጋለብኩኝ ነው› ብሎ እንደ ቁራ እየለፈፈ በተግባር ግን፡- መብራት፣ ውሃ፣ መንገድ፣ ኔት-ወርክ እንደ አደይ አበባ በዓመት አንዴ ብቻ ብቅ የሚለው? በአገልግሎት ተቋማት መጠቀምስ እንዲህ የአሲምባን ያህል ያራቀው ማን ነው? ፍትሕን የጠሉትን መበቀያ መሳሪያ አድርገው ያረከሱት እነማን ናቸው? ሰርቶ መብላት የማይጨበጥ ጉም የሆነብንስ በማን የተነሳ ነው? …በርግጥ ይህንን ጥያቄ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ብናቀርብለት እንደ መለስ ዜናዊ በተረት መሳለቁ ባይሆንለትም፣ ‹‹ሰለሜ ሰለሜ››ን እየጨፈረ፤ እነ‹‹ሚካኤል ስሁል›› በቀደዱለት ልክ ዳናኪራውን እያስነካው ‹‹ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም!›› ብሎ ከመዘባበት አይመለስም፡፡ መቼስ እንደዚህ ሕዝብ የተናቀ የትም አይገኝም፡፡
ኢህአዴግ መፍረስ ያለበት ለምንድን ነው?
‹‹አንተ ሌዎናርዶ የሮማ ጅል
የሰራሀትን ልታሻሽል
ልታፈርሳት ልትገነባት
ደግመህ ደጋግመህ ልትሰራት
ሰልሰህ ልትሰራት ስትችል
ጣኦት አደረግካት በሞትህ አጉል አጉል
ለራስህ ፍጡር እግዚኦ ልትል››
ይህ ግጥም በሰፈረበት ገፅ ላይ የተጠቀሰው የግርጌ ማስታወሻ ደግሞ ሊተላለፍ የተፈለገውን መልዕክት እንዲህ በማለት አብራርቶታል፡-
ታዬ የሚባል የኢህአፓ ታጋይ ‹ራሳችን የፈጠርነውን ድርጅት ማስተካከል አለብን› የሚል እምነት የነበረው ሲሆን፣ ዳ ቪንቺ እራሱ ለሳላት ሞናሊዛ ፍቅር እንደተማረከ ሁሉ እኛም የፈጠርነውንና የተበላሸውን ድርጅት አመለክነው፤ ማስተካከልም ተሳነን በማለት ፓርቲው ላይ እምነት ማጣቱን ‹ሞናሊዛ› በሚል ርዕስ በፃፈው ውብ ግጥም ገለፀ፡፡  (ገፅ 61)
እነሆም አብዮታዊ ግንባሩ፣ ከመስራቾቹ አንዱ የሆነው ኢህዴን/ብአዴን፣ ያን ጊዜ ኢህአፓን መክሰሻ ባደረገበት ‹‹ድርጅታዊ አምልኮ›› ራሱም ተጠልፎ ከወደቀ ዓመታት ነጉደዋል፡፡ ታዬ እንዳለውም መሪዎቹ ኢህአዴግን ናቡከደናፆር አሰርቶት እንደነበረው አይነት እጅግ ግዙፍ ‹‹አምላክ›› (ጣኦት) አድርገው ሀገርና ሕዝብን እየገበሩለት (እየሰዉለት) ነው፡፡ ርዕዮተ-ዓለምም ሆነ ፖሊሲ (በተለይ መሬትን በተመለከተ) ‹‹የሚቀየረው በመቃብራችን ላይ ነው›› ሲሉም አስረግጠው ተናግረዋል፡፡ የትምህርት ፖሊሲውም እንዲህ ትውልድን እየገደለም እንዲሻሻል ያልተሞከረው በዚሁ እምነታቸው ይመስለኛል፡፡ ይህ ሁኔታም ነው እናንተም የምትስማሙባቸውን ታላላቅ ሀገራዊ ችግሮችን ለመፍታት ኢህአዴግን ከማፍረስ ውጪ አማራጭ እንዳይኖር ያደረገው፡፡
ከእንግዲህ ወዲያም ከጥፋቱ ታርሞ ለሀገር የሚጠቅም ዲሞክራሲያዊ የህዝብ ሥርዓት ሊያነበር ይችላል ብሎ ተስፋ ማድረግ ተላላነት ነው፡፡ እንኳን እናንተ ከተማ ላይ የተቀላቀላችሁት አባላት ቀርቶ፣ ከበርሃ አቅፈው ደግፈው እዚህ ያደረሱት አንጋፋ ታጋዮችና አንዳንድ አመራሮቹም በድርጅቱ ተስፋ ቆርጠው ጥለውት መሄድ ከጀመሩ ሰንብቷል፡፡ ታጋይ የውብዳር አስፋው ‹‹ፊኒክሷም ሞታ ትነሳለች›› በሚለው መጽሐፏ እውነታውን እንዲህ በማለት ገልፀዋለች፡- ‹‹የድርጅቱ አመራር የወሰዳቸውን የተሳሳቱ እርምጃዎች ቀድሞ ከነበረኝ የድርጅቱ ግንዛቤ ጋር በማጣመር ለዓመታት የታገሉለትንና የደከሙለትን አባላት በነፃ እንዲንቀሳቀሱ ያላስቻለ ድርጅት፣ ለሕዝብ ነፃነትና ለዲሞክራሲ እታገላለሁ ቢል ከይስሙላ የማያልፍ ከንቱ መፈክር መሆኑን ደምድሜ፣ ከመጋቢት 5 ቀን 1993 ዓ.ም ጀምሮ ራሴን ከድርጅቱ አገለልኩ፡፡ ይህም በሕይወቴ ጉዞ ዋነኛውና ወሳኝ እርምጃ ነበር፡፡›› (ገፅ 16)
እንግዲህ ከ1968 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የድርጅት፣ የሴቶች ጉዳይና የመንግስት ሥራዎች ተሰማርታ ልጅነቷን በትግል የጨረሰችው የአቶ ገብሩ አስራት ባለቤት፣ የውብዳር አስፋው እንዲህ አይነቱን ከባድ ውሳኔ በማሳለፍ ከኢህአዴግ ከተቆራረጠች እነሆ አስራ ሶስት ዓመታት ነጉደዋል፡፡ በግልባጩ እናንተ ደግሞ እስካሁን ድረስ አንቀላፍታችኋል-ገና አልነቃችሁም፡፡ እናም እውነት እውነት እላችኋለሁ፡- ከዚህ በላዔ-ሰብ ሥርዓት ለመገላገል የምንችለው፣ ዛሬውኑ ይህንን ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ዋነኛና ወሳኝ እርምጃ በቆራጥነት መውሰድ ስትችሉ ብቻ ነው፡፡ አለበለዚያ…
(የዚህ ጽሑፍ ሃሰበ-መልዕክትን በቅንነት ትቀበሉታላችሁ በሚል መተማመን አፈፃፀሙን፡- በምን አይነት መንገድ ተቀራርበን ልንወያይ እንችላለን? በየትኞቹ ጉዳዮች ላይ መግባባት ይቻላል? ሃሳቡንስ ከግብ ለማድረስ ምን ያህል ጊዜ ይወስዳል? የሚሉትንና መሰል ጥያቄዎችን በሌላ ዕትም ተገናኝተን በስፋት እንመክርባቸዋለን)
አትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

የቀድሞው የጋምቤላ ፕሬዚዳንት ደቡብ ሱዳን ከሆቴል ውስጥ ታፈኑ “ወያኔ እጅ ገብተዋል”

የጋምቤላ ክልልን ሲመሩ ቆይተው ባለመስማማት የኮበለሉት የቀድሞው የክልሉ ፕሬዚዳንት ደቡብ ሱዳን ከሆቴል ውስጥ ታፍነው መወሰዳቸው ተጠቆመ። ዜናው በገለልተኛ ወገን ባይገለጽም ኖርዌይ በስደት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ይኖሩ የነበሩት አቶ ኦኬሎ አኳይ በኢህአዴግ በጥብቅ የሚፈለጉ ሰው ነበሩ።
በመለስ ዜናዊ ውሳኔ በአኙዋክ ተወላጆች ላይ በጅምላ የተከናወነውን ጭፍጨፋ አስመልከቶ ተቃውሞ በማሰማት የኮበለሉት አቶ ኦኬሎ ወደ ደቡብ ሱዳን ከማምራታቸው በፊት ኬንያ እንደነበሩ፣ ከኬንያ ወደ ደቡብ ሱዳን ለምን እንደተጓዙ የዜናው ምንጮች በይፋ ከመናገር ተቆጥበዋል።
ስማቸው እንዲደበቅላቸው የጠየቁ የጋምቤላ አስተዳደር ባልደረባ ለጎልጉል የአካባቢው ዘጋቢ እንደተናገሩት አቶ ኦኬሎ ደቡብ ሱዳን ሆቴል በተቀመጡበት መታፈናቸውን አረጋግጠዋል። “ወያኔ እጅ ገብቷል” ሲሉ ያከሉት እኚሁ ሰው “አቶ ኦኬሎ ብረት በማንሳት ወያኔን ለመታገል ከተነሱ ጋር ተቀላቅለዋል በሚል ስማቸው መመዝገቡንና ወደ ደቡብ ሱዳን ማቅናታቸው በመታወቁ ህወሃቶች እጅ ሊወድቁ ችለዋል” ብለዋል። ምንጩ ይህንን ይበሉ እንጂ አቶ ኦኬሎ አክዋይ ወደ ደቡብ ሱዳን ያቀኑበትን ምክንያት በርግጠኛነት ሃላፊነት ወስዶ የገለጸ ወገን አልተደመጠም። ኢህአዴግም ቢሆን የቀድሞውን ሹመኛ ስለመያዙ ይፋ ያደረገው ነገር የለም።
ከደቡብ ሱዳን ቀውስ ጋር በተያያዘ የኑዌር ተወላጅ ከሆኑት ሬክ ማቻር ጦር ጋር በመሰለፍ የሳልቫ ኪርን ሃይል ሲወጉ ከተገደሉ ወታደሮች መካከል የኢህአዴግን ሰራዊት መለያ የለበሱ ኑዌሮች መገኘታቸው ውዝግብ አስነስቶ እንደነበር ያመለከቱት ምንጭ “ደቡብ ሱዳን እየወጋት ካለው ኢህአዴግ ጋር አብራ የቀድሞውን የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳደር ከምድሯ ላይ እንዲታፈኑ መፍቀዷ ቅሬታ ያስነሳል” ብለዋል።
ከቤተሰባቸው ተነጥለው በስደት ከሚኖሩበት ኖርዌይ ወደ ደቡብ ሱዳን ያመሩት የቀድሞው የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳድር ደቡብ ሱዳን በህወሃት ሙሉ ቁጥጥርና ፈቃድ የምትንቀሳቀስ አገር መሆኗን እያወቁ ወደዛ ማቅናታቸውን ባሥልጣኑ “ታላቅ ጥፋት” ብለውታል። ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። በቅርቡ አቶ ኦሞት ኦባንግ መኮብለላቸውና በብዙዎች ዘንድ አውሮጳ እንዳሉ ቢነገርም በትክክል ያሉበት አገር በይፋ አለመታወቁን መዘገባችን ይታወሳል።

ኢህአዴግ የእምነት ተቋማትን በጥብቅ የሚቆጣጠርበት ህግ ሊያጸድቅ ነው

ህጉ ጣጣ እንዳያመጣ የሰጉ ኢህአዴግን እየመከሩ ነው
religions
ኢትዮጵያን ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ እየገዛ ያለው ኢህአዴግ የሃይማኖት ተቋማትንና ምዕመናኑን በጥብቅ የሚቆጣጠርበትን ህግ ለማጽደቅ በዝግጅት ላይ መሆኑ ተሰማ። የህጉ ረቂቅ የደረሳቸው ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ኢህአዴግን አበክረው እየመከሩና በሚያመጣው አጠቃላይ መዘዝ ዙሪያ እያስጠነቀቁ ነው።
ጎልጉል ከዲፕሎማት ምንጮቹ ባገኘው መረጃ መሰረት ኢህአዴግ በእምነት ተቋማት ላይ ቁጥጥሩን የሚያጠብቅበትንና ከሃይማኖት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውጭ መሰብሰብን፣ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግንና የተቃውሞ ድምጽ ማሰማትን የሚከለክል ህግ አዘጋጅቷል።
የዜናው ምንጮች ዝርዝር ህጉን ለጊዜው ይፋ ከማድረግ እንደሚቆጠቡ አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ የሚደነገገውን አዲስ ህግ ጥሰዋል በሚል የሚከሰሱ ምዕመኖች እስከ እድሜ ልክ በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ የሚያዝ አንቀጽ አለበት። አዲሱ ህግ ከሽብርተኞች ህግ ጋር የሚጣቀስ እንደሆነም የጠቆሙት ክፍሎች ኢህአዴግ “ከእምነት ነጻነት” ጥያቄ ጋር በተያያዘና በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ ውስጥ ውስጡን እየነደደ ያለው ችግር ስላስጨነቀው ይህንን ህግ ለማውጣት መገደዱን አስረድተዋል። በሌላ በኩልም እስካሁን መፍትሔ ያላገኘው የሙስሊሞች ጥያቄ ከዚያም ጋር ተከትሎ የተከሰተው ደም መፋሰስ ወደፊት ሊያመጣ በሚችለው ጉዳይ ላይ ኢህአዴግን በብርቱ አሳስቦታል፡፡
ኢህአዴግ ከቀን ወደ ቀን ቀውስ እየተደራረበት እንደሆነ የተረዳችው አሜሪካ በከፍተኛ ባለስልጣኖቿ አማካይነት ኢህአዴግን እየመከረች እንደሆነ ከዲፕሎማቶች የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ከፖለቲካው ቀውስና በቀጠናው ካለው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ አሜሪካ በተደጋጋሚ የህወሃትን ሰዎች በተናጠል እያነጋገረች እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል። ዲፕሎማቶቹ እንደሚሉት አሜሪካ መለስ “ከተሰዉ” በኋላ አገሪቱን ማን እየመራት እንደሆነ በቅጡ ለመረዳት በሚያስቸግር ሁኔታ የስልጣን መዛነፍና ደረጃን የጠበቀ የስልጣን ተዋረድ አለመኖሩም አሳስቧታል። ኢህአዴግ ለህልውናዬ ያሰጋኛል በሚል መንግሥታዊ ባልሆኑ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች /መያዶች/ ላይ ያወጣውን አፋኝ ህግም ጠቅሰዋል። ዲፕሎማቶቹ በጉዳዩ ዙሪያ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት ወቅቱ አሁን እንዳልሆነ አመልክተዋል።

fredag 28. mars 2014

Ethiopian Journalists Forum (EJF) warns leaders of three Journalists Associations

March 28, 2014
by Betre Yacob
Ethiopian Journalists Forum (EJF), the newly established journalists association in Ethiopia, warned leaders of three journalists associations operating in the country.Ethiopian Journalists Forum is a nonpartisan and independent professional association
In a statement issued yesterday, the association accused the officials of Ethiopian journalists Association (EJA), Ethiopian National Journalists Union (ENJU), and Ethiopian Free Journalists Association (EFJA) of fabricating false accusations against the association and members of media organizations.
Ethiopian Journalists Forum is a nonpartisan and independent professional association intended to defend the freedom of speech and of the press in Ethiopia.
The press statement says that the officials have been deliberately engaged in fabricating false accusations ranging from terrorism to conspiracy— aiming to intimidate journalists and members of the association. “They are trying to spoil the name of our association, which is getting a wider acceptance among journalists and media workers”, the statement explains.
“For instance, in an interview published at Addis Admass weekly newspaper issued on March 30, 2014 they said that journalists had been preparing to commit terrorism against the nation and its citizens. They also accused two unnamed countries of backing the journalists. In another article published at Reporter, a weekly newspaper, issued on March 9, 2014 they once again said the same thing accusing journalists”, it further explains.
The statement says the association doesn’t have a response for the groundless accusations of these depraved individuals—who are barking to retain their own cheep benefits. It says it only would like to warn them once and for all to refrain from their unlawful acts.
The EJF was established on 20 January, 2014 considering the harsh working conditions of journalists in Ethiopia; and the importance of a unified media workers and journalists’ voice. In a few months only, the association has been able to get acceptance among journalists and media institutions.
Particularly, the EJF has been welcomed by almost all journalists operating in the free press. Its formation has been good news to those who wish to see an independent institution—which is loyal only to the journalists.
The EJF is supposed by many to be a best framework to work against the deteriorating press freedom in the country and bring about change on the safety of journalists. It is, however, seen as a threat by EJA, ENJU, and EFJA. According to the association, it has begun to experience their accusation since its inception.
The EJF has a vision to become a leading professional association in Ethiopia, which defends the freedom of speech and of the press as well as the rights of journalists.
The Wake of Non-operational Associations
Ethiopian journalists Association (EJA), Ethiopian National Journalists Union (ENJU), and Ethiopian Free Journalists Association (EFJA) were in active for a long period. They came to the stage following the formation of EJF.
Both the associations are accused of being loyal to the regime and of failing to play their role. None of them have ever been seen doing anything to bring about change on the deteriorating press freedom and safety of journalists.
Despite the fact that journalists are still subjected to violence, EJA, ENJU, and EFJA believe freedom of speech and of the press is respected in Ethiopia, and accuse CPJ and other international organizations of defaming the name of the country.
They also accuse Ethiopian journalists of using their rights to incite violence in the country. They even don’t accept the journalists, who are currently behind the bar in the country, are prosecuted because of their job.

የወያኔን ከፋፋይ አገዛዝ እናምክን


የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰብ ሊከበርላቸውና ሊያሳድጋቸው የሚገቡ የተለያዩ የባህልና የታሪክ ቅርሶች ያሏቸውን ያህል በብዙ መንገድ የሚያይዝ የጋራ ታሪክ ቅርስና ዝምድና አላቸው። ልዩነቶቹ ራሳቸው ተጠቃቃሚ ለሆነ የእርስበርስ ግንኙነታቸው ጠቃሚ እንጂ ከአንድ ሀገር ማህበረሰብነታቸውና ከጋራ ህልማቸው ጋር የሚጋጩ የጠብና የግጭት መንስኤዎች አይደሉም። ከጠብና ግጭት ማንኛውም ብሄር ብሄረሰብ ተጠቃሚ አይደለም። ከጠብና ግጭት ጥቅም ይገኛል ብለው የሚያስቡ “ግርግር ለሌባ ይመቻል” የሚለውን የወሮ በላ ፍልስፍና የሚከተሉ የቀን ጅቦች እንጂ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች አይደሉም። በወያኔ የግዛት ዘመን የደረሱትን ግጭቶች መፈናቅሎችና የተፈጠሩትን የእርስበርስ ጥርጣሬዎችን ልብ ብሎ ለተመለከተ ሁሉም በአገዛዙ እና በሎሌ የበታች ሹማምንቱ የተፈጠሩ እንጂ አንድም ጊዜ እንኳን ከህዝብ የመነጩ አይደሉም።
የወያኔ ጉጅሌ በአገዛዝ ዘመኑ ሁሉ ብሄር ብሄረሰቦችን ከሚያይዟቸው የጋራ ማህበራዊ ቅርሶችና ህልሞች ይልቅ ካለመታከት ልዩነቶቻችን ላይ ያተኮረ ፖለቲካ እያካሄደ እንዳለ ግልጽ ነው። ከዚህ አልፎም አዳዲስ የእርስበርስ ግጭቶችን እና ጠቦች እንዲፈጠሩ ተግቶ የሚሰራ ከፋፋይ ቡድን ነው። እርስበርሱ መጠራጠርና መፈራራት እንዲሰፍን ልዩ ልዩ ስልቶችን ይቀይሳል። ከአንዱ ብሄረሰብ ተንኳሽ አዘጋጅቶ ሌላው ብሄረሰብ ላይ አደጋ እንዲደርስ ከዚያም ተጠቃሁ የሚለው አጸፋ እንዲመልስ ያደርጋል። የአንዱን ብሄረሰብ መንደርና ንeበረት በእሳት ለኩሶ በሌላው ብሄረሰብ እንዲመካኝ ያድርጋል። አንዱ በአንዱ ላይ እንዲያማርር ከንፈሩን እንዲነክስ ማድረግ ለወያኔ ጉጅሌዎችና ለሎሌዎቻቸው እንደፖለቲካ ጥበብ ከታየ ሁለት አስርት አመታት አልፈዋል። በየትኛውም የሀገራችን አካባቢዎች የተቀሰቀሱ የርስበርስ ጥርጣሬዎችና ግጭቶችን ያሸተተ ሁሉ ወያኔ፣ ወያኔ እንደሚገሙ ያረጋገጠው ጉዳይ ነው።
ወያኔዎች የኢትዮጵያን ብሄር ብሄረሰቦች ከፋፍለውና ከቻሉም አጋጭተው ካልሆነ በስተቀር የዝርፊየ ኢኮኖሚያቸውን መቀጠል እንደማይችሉ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች የጋራ ጥቅማቸውንና ህልማቸውን ይዘው የተነሱ እለት ወያኔ ያከተመለት መሆኑን ያውቃል። ለዚህም ነው በየክልሉ እና ዞኑ በፍጹም ከሆዳቸውና ጥቅማቸው በላይ ማሰብ የማይችሉ ግለሰቦችን ከየብሄረሰቡ እየመረጠ የሚሾምልን። ወያኔ ነጻ የህዝብ ምርጫ የሚፈራው ለዚህ ማረጋገጫ ነው፡፡
የወያኔ ጉጅሌዎች ከጊዚያዊ ጥቅም በዘለለ ማሰብ ስለተሳናቸው እንጂ ይህ አካሄዳቸው ለራሳቸውም ለዘለቄታው የማይጠቅም መሆኑን ዘንግተውታል። በልዩነታችን ላይ መጫወት ማለት በእሳት እንደ መጫወት የማይመስላቸው ለዚህም ነው። ይህ የተጀመረው እሳት ራሳቸውንም አይምርም።
ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ መላው የኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰቦች የጋራ ግብና የተሻለው የነገ ነጻነት ተስፋቸው የሚረጋገጠው በጋራና እጅ ለእጅ ተያይዘው በሚያደርጉት ትግል ብቻ ነው ብሎ ያምናል። ለዚህ የወያኔ መሰሪ የከፋፍለህና አጋጭተህ ግዛ ተንኮል ራሳችንን እንዳናመቻች የገዛ መከራችንን ማራዘሚያ እድል ለዘራፊ ገዥዎቻችን እንዳንሰጥና ለጋራ ህልማችን እንድንቆም ጥሪውን ያቀርባል።
የወያኔ ጉጅሌ ሆን ብሎ በቀጥታና በተዘዋዋሪ የኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰቦች እንዲጋጩ፣ እርስበርስ በጥርጣሬ እንዲተያዩና እንዲፈራሩ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት ድርጊቱ በእሳት መጫወት መሆኑን አውቆ ከዚህ እኩይ ተግባር እንዲታቀብ ግንቦት 7 እያሳሰበ በማንኛውም ሁኔታ በማህበረሰቦች መካከል ለሚደርስ ግጭትና ጉዳት ሙሉ ሀላፊነቱ የወያኔና የወያኔ ብቻ መሆኑን አጥብቆ ያስገነዝባል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

onsdag 26. mars 2014

Ethiopia spies on citizens with foreign technology: HRW



AFP – Ethiopia is using foreign technology to spy on citizens suspected of being critical of the government, Human Rights Watch said in a report released Tuesday.
Ethiopia is using foreign technology to spy on citizens
The report accused the government of using Chinese and European technology to survey phone calls and Internet activity in Ethiopia and among the diaspora living overseas, and HRW said firms colluding with the government could be guilty of abuses.
“The Ethiopian government is using control of its telecom system as a tool to silence dissenting voices,” HRW’s business and human rights director Arvind Ganesan, said in a statement.
“The foreign firms that are providing products and services that facilitate Ethiopia’s illegal surveillance are risking complicity in rights abuses.”
The Ethiopian government dismissed the report as “mud-slinging” and accused the rights watchdog of repeatedly unfairly targeting the country.
“This is one of the issues that it has in the list of its campaigns to smear Ethiopia’s image, so there is nothing new to respond to it, because there is nothing new to it,” Ethiopia’s Information Minister, Redwan Hussein, told AFP.
He said Ethiopia is committed to improving access to telecommunications as part of its development program, not as a means to increase surveillance.
“The government is trying its level best to create access to not only to the urban but to all corners of the country,” Redwan added.
Ethiopia’s phone and internet networks are controlled by the state-owned Ethio Telecom, the sole telecommunications provider in the country.
HRW said the government’s telecommunications monopoly allows it to readily monitor user activity.
“Security officials have virtually unlimited access to the call records of all telephone users in Ethiopia. They regularly and easily record phone calls without any legal process or oversight,” the report said.
The rights watchdog said information gathered was often used to garner evidence against independent journalists and opposition activists, both inside Ethiopia and overseas.
In February, a US man filed a lawsuit against the Ethiopian government, accusing authorities of infecting his computer with spyware to monitor his online activity.
Rights groups have accused Ethiopia of cracking down on political dissenters, independent media and civil society through a series of harsh laws, including anti-terrorism legislation.
Only about 23 percent of Ethiopia’s 91 million people subscribe to mobile phones, and less than one percent have access to mobile internet, according to the International Telecommunications Union.
The government has committed to increasing mobile access by 2015, as part of an ambitious development plan.
Ethiopia has hired two Chinese firms, ZTE and Huawei, to upgrade the mobile network across the country.
———————
Human Right Watch Full Report

Ethiopia: Telecom Surveillance Chills Rights

Foreign Technology Used to Spy on Opposition inside Country, Abroad
(Berlin) – The Ethiopian government is using foreign technology to bolster its widespread telecom surveillance of opposition activists and journalists both in Ethiopia and abroad, Human Rights Watch said in a report released today.
The 100-page report“‘They Know Everything We Do’: Telecom and Internet Surveillance in Ethiopia,” details the technologies the Ethiopian government has acquired from several countries and uses to facilitate surveillance of perceived political opponents inside the country and among the diaspora. The government’s surveillance practices violate the rights to freedom of expression, association, and access to information. The government’s monopoly over all mobile and Internet services through its sole, state-owned telecom operator, Ethio Telecom, facilitates abuse of surveillance powers.
“The Ethiopian government is using control of its telecom system as a tool to silence dissenting voices,” said Arvind Ganesan, business and human rights director at Human Rights Watch. “The foreign firms that are providing products and services that facilitate Ethiopia’s illegal surveillance are risking complicity in rights abuses.”
The report draws on more than 100 interviews with victims of abuses and former intelligence officials in Ethiopia and 10 other countries between September 2012 and February 2014. Because of the government’s complete control over the telecom system, Ethiopian security officials have virtually unlimited access to the call records of all telephone users in Ethiopia. They regularly and easily record phone calls without any legal process or oversight.
Recorded phone calls with family members and friends – particularly those with foreign phone numbers – are often played during abusive interrogations in which people who have been arbitrarily detained are accused of belonging to banned organizations. Mobile networks have been shut down during peaceful protests and protesters’ locations have been identified using information from their mobile phones.
A former opposition party member told Human Rights Watch: “One day they arrested me and they showed me everything. They showed me a list of all my phone calls and they played a conversation I had with my brother. They arrested me because we talked about politics on the phone. It was the first phone I ever owned, and I thought I could finally talk freely.”
The government has curtailed access to information by blocking websites that offer any independent or critical analysis of political events in Ethiopia. In-country testing that Human Rights Watch and Citizen Lab, a University of Toronto research center focusing on internet security and rights, carried out in 2013 showed that Ethiopia continues to block websites of opposition groups, media sites, and bloggers. In a country where there is little in the way of an independent media, access to such information is critical.
Ethiopian authorities using mobile surveillance have frequently targeted the ethnic Oromo population. Taped phone calls have been used to compel people in custody to confess to being part of banned groups, such as the Oromo Liberation Front, which seeks greater autonomy for the Oromo people, or to provide information about members of these groups. Intercepted emails and phone calls have been submitted as evidence in trials under the country’s flawed anti-terrorism law, without indication that judicial warrants were obtained.
The authorities have also detained and interrogated people who received calls from phone numbers outside of Ethiopia that may not be in Ethio Telecom databases. As a result, many Ethiopians, particularly in rural areas, are afraid to call or receive phone calls from abroad, a particular problem for a country that has many nationals working in foreign countries.
Most of the technologies used to monitor telecom activity in Ethiopia have been provided by the Chinese telecom giant ZTE, which has been in the country since at least 2000 and was its exclusive supplier of telecom equipment from 2006 to 2009. ZTE is a major player in the African and global telecom industry, and continues to have a key role in the development of Ethiopia’s fledgling telecom network. ZTE has not responded to Human Rights Watch inquiries about whether it is taking steps to address and prevent human rights abuses linked to unlawful mobile surveillance in Ethiopia.
Several European companies have also provided advanced surveillance technology to Ethiopia, which have been used to target members of the diaspora. Ethiopia appears to have acquired and used United Kingdom and Germany-based Gamma International’s FinFisher and Italy-based Hacking Team’s Remote Control System. These tools give security and intelligence agencies access to files, information, and activity on the infected target’s computer. They can log keystrokes and passwords and turn on a device’s webcam and microphone, effectively turning a computer into a listening device. Ethiopians living in the UK, United States, Norway, and Switzerland are among those known to have been infected with this software, and cases have been brought in the US and UK alleging illegal wiretapping. One Skype conversation gleaned from the computers of infected Ethiopians has appeared on pro-government websites.
Gamma has not responded to Human Rights Watch inquiries as to whether it has any meaningful process in place to restrict the use or sale of these products to governments with poor human rights records. While Hacking Team applies certain precautions to limit abuse of its products, it has not confirmed whether and how those precautions applied to sales to the Ethiopian government.
“Ethiopia’s use of foreign technologies to target opposition members abroad is a deeply troubling example of this unregulated global trade, creating serious risks of abuse,” Ganesan said. “The makers of these tools should take immediate steps to address their misuse; including investigating the use of these tools to target the Ethiopian diaspora and addressing the human rights impact of their Ethiopia operations.”
Such powerful spyware remains virtually unregulated at the global level and there are insufficient national controls or limits on their export, Human Rights Watch said. In 2013, rights groups filed a complaint at the Organization for Economic Co-operation and Development alleging such technologies had been deployed to target activists in Bahrain, and Citizen Lab has found evidence of use of these tools in over 25 countries.
The internationally protected rights to privacy, and freedom of expression, information, and association are enshrined in the Ethiopian constitution. However, Ethiopia either lacks or ignores judicial and legislative mechanisms to protect people from unlawful government surveillance. This danger is made worse by the widespread use of torture and other ill-treatment against political detainees in Ethiopian detention centers.
The extent of Ethiopia’s use of surveillance technologies may be limited by capacity issues and a lack of trust among key government ministries, Human Rights Watch said. But as capacity increases, Ethiopians may increasingly see far more pervasive unlawful use of mobile and email surveillance.
The government’s actual control is exacerbated by the perception among many Ethiopians that government surveillance is omnipresent, resulting in considerable self-censorship, with Ethiopians refraining from openly communicating on a variety of topics across telecom networks. Self-censorship is especially common in rural Ethiopia, where mobile phone coverage and access to the Internet is very limited. The main mode of government control is through extensive networks of informants and a grassroots system of surveillance. This rural legacy means that many rural Ethiopians view mobile phones and other telecommunications technologies as just another tool to monitor them, Human Rights Watch found.
“As Ethiopia’s telecom system grows, there is an increasing need to ensure that proper legal protections are followed and that security officials don’t have unfettered access to people’s private communications,” Ganesan said. “Adoption of Internet and mobile technologies should support democracy, facilitating the spread of ideas and opinions and access to information, rather than being used to stifle people’s rights.”
Source. ECADEF

Ethiopia spies on citizens with foreign technology: HRW



AFP – Ethiopia is using foreign technology to spy on citizens suspected of being critical of the government, Human Rights Watch said in a report released Tuesday.
Ethiopia is using foreign technology to spy on citizens
The report accused the government of using Chinese and European technology to survey phone calls and Internet activity in Ethiopia and among the diaspora living overseas, and HRW said firms colluding with the government could be guilty of abuses.
“The Ethiopian government is using control of its telecom system as a tool to silence dissenting voices,” HRW’s business and human rights director Arvind Ganesan, said in a statement.
“The foreign firms that are providing products and services that facilitate Ethiopia’s illegal surveillance are risking complicity in rights abuses.”
The Ethiopian government dismissed the report as “mud-slinging” and accused the rights watchdog of repeatedly unfairly targeting the country.
“This is one of the issues that it has in the list of its campaigns to smear Ethiopia’s image, so there is nothing new to respond to it, because there is nothing new to it,” Ethiopia’s Information Minister, Redwan Hussein, told AFP.
He said Ethiopia is committed to improving access to telecommunications as part of its development program, not as a means to increase surveillance.
“The government is trying its level best to create access to not only to the urban but to all corners of the country,” Redwan added.
Ethiopia’s phone and internet networks are controlled by the state-owned Ethio Telecom, the sole telecommunications provider in the country.
HRW said the government’s telecommunications monopoly allows it to readily monitor user activity.
“Security officials have virtually unlimited access to the call records of all telephone users in Ethiopia. They regularly and easily record phone calls without any legal process or oversight,” the report said.
The rights watchdog said information gathered was often used to garner evidence against independent journalists and opposition activists, both inside Ethiopia and overseas.
In February, a US man filed a lawsuit against the Ethiopian government, accusing authorities of infecting his computer with spyware to monitor his online activity.
Rights groups have accused Ethiopia of cracking down on political dissenters, independent media and civil society through a series of harsh laws, including anti-terrorism legislation.
Only about 23 percent of Ethiopia’s 91 million people subscribe to mobile phones, and less than one percent have access to mobile internet, according to the International Telecommunications Union.
The government has committed to increasing mobile access by 2015, as part of an ambitious development plan.
Ethiopia has hired two Chinese firms, ZTE and Huawei, to upgrade the mobile network across the country.
———————
Human Right Watch Full Report

Ethiopia: Telecom Surveillance Chills Rights

Foreign Technology Used to Spy on Opposition inside Country, Abroad
(Berlin) – The Ethiopian government is using foreign technology to bolster its widespread telecom surveillance of opposition activists and journalists both in Ethiopia and abroad, Human Rights Watch said in a report released today.
The 100-page report“‘They Know Everything We Do’: Telecom and Internet Surveillance in Ethiopia,” details the technologies the Ethiopian government has acquired from several countries and uses to facilitate surveillance of perceived political opponents inside the country and among the diaspora. The government’s surveillance practices violate the rights to freedom of expression, association, and access to information. The government’s monopoly over all mobile and Internet services through its sole, state-owned telecom operator, Ethio Telecom, facilitates abuse of surveillance powers.
“The Ethiopian government is using control of its telecom system as a tool to silence dissenting voices,” said Arvind Ganesan, business and human rights director at Human Rights Watch. “The foreign firms that are providing products and services that facilitate Ethiopia’s illegal surveillance are risking complicity in rights abuses.”
The report draws on more than 100 interviews with victims of abuses and former intelligence officials in Ethiopia and 10 other countries between September 2012 and February 2014. Because of the government’s complete control over the telecom system, Ethiopian security officials have virtually unlimited access to the call records of all telephone users in Ethiopia. They regularly and easily record phone calls without any legal process or oversight.
Recorded phone calls with family members and friends – particularly those with foreign phone numbers – are often played during abusive interrogations in which people who have been arbitrarily detained are accused of belonging to banned organizations. Mobile networks have been shut down during peaceful protests and protesters’ locations have been identified using information from their mobile phones.
A former opposition party member told Human Rights Watch: “One day they arrested me and they showed me everything. They showed me a list of all my phone calls and they played a conversation I had with my brother. They arrested me because we talked about politics on the phone. It was the first phone I ever owned, and I thought I could finally talk freely.”
The government has curtailed access to information by blocking websites that offer any independent or critical analysis of political events in Ethiopia. In-country testing that Human Rights Watch and Citizen Lab, a University of Toronto research center focusing on internet security and rights, carried out in 2013 showed that Ethiopia continues to block websites of opposition groups, media sites, and bloggers. In a country where there is little in the way of an independent media, access to such information is critical.
Ethiopian authorities using mobile surveillance have frequently targeted the ethnic Oromo population. Taped phone calls have been used to compel people in custody to confess to being part of banned groups, such as the Oromo Liberation Front, which seeks greater autonomy for the Oromo people, or to provide information about members of these groups. Intercepted emails and phone calls have been submitted as evidence in trials under the country’s flawed anti-terrorism law, without indication that judicial warrants were obtained.
The authorities have also detained and interrogated people who received calls from phone numbers outside of Ethiopia that may not be in Ethio Telecom databases. As a result, many Ethiopians, particularly in rural areas, are afraid to call or receive phone calls from abroad, a particular problem for a country that has many nationals working in foreign countries.
Most of the technologies used to monitor telecom activity in Ethiopia have been provided by the Chinese telecom giant ZTE, which has been in the country since at least 2000 and was its exclusive supplier of telecom equipment from 2006 to 2009. ZTE is a major player in the African and global telecom industry, and continues to have a key role in the development of Ethiopia’s fledgling telecom network. ZTE has not responded to Human Rights Watch inquiries about whether it is taking steps to address and prevent human rights abuses linked to unlawful mobile surveillance in Ethiopia.
Several European companies have also provided advanced surveillance technology to Ethiopia, which have been used to target members of the diaspora. Ethiopia appears to have acquired and used United Kingdom and Germany-based Gamma International’s FinFisher and Italy-based Hacking Team’s Remote Control System. These tools give security and intelligence agencies access to files, information, and activity on the infected target’s computer. They can log keystrokes and passwords and turn on a device’s webcam and microphone, effectively turning a computer into a listening device. Ethiopians living in the UK, United States, Norway, and Switzerland are among those known to have been infected with this software, and cases have been brought in the US and UK alleging illegal wiretapping. One Skype conversation gleaned from the computers of infected Ethiopians has appeared on pro-government websites.
Gamma has not responded to Human Rights Watch inquiries as to whether it has any meaningful process in place to restrict the use or sale of these products to governments with poor human rights records. While Hacking Team applies certain precautions to limit abuse of its products, it has not confirmed whether and how those precautions applied to sales to the Ethiopian government.
“Ethiopia’s use of foreign technologies to target opposition members abroad is a deeply troubling example of this unregulated global trade, creating serious risks of abuse,” Ganesan said. “The makers of these tools should take immediate steps to address their misuse; including investigating the use of these tools to target the Ethiopian diaspora and addressing the human rights impact of their Ethiopia operations.”
Such powerful spyware remains virtually unregulated at the global level and there are insufficient national controls or limits on their export, Human Rights Watch said. In 2013, rights groups filed a complaint at the Organization for Economic Co-operation and Development alleging such technologies had been deployed to target activists in Bahrain, and Citizen Lab has found evidence of use of these tools in over 25 countries.
The internationally protected rights to privacy, and freedom of expression, information, and association are enshrined in the Ethiopian constitution. However, Ethiopia either lacks or ignores judicial and legislative mechanisms to protect people from unlawful government surveillance. This danger is made worse by the widespread use of torture and other ill-treatment against political detainees in Ethiopian detention centers.
The extent of Ethiopia’s use of surveillance technologies may be limited by capacity issues and a lack of trust among key government ministries, Human Rights Watch said. But as capacity increases, Ethiopians may increasingly see far more pervasive unlawful use of mobile and email surveillance.
The government’s actual control is exacerbated by the perception among many Ethiopians that government surveillance is omnipresent, resulting in considerable self-censorship, with Ethiopians refraining from openly communicating on a variety of topics across telecom networks. Self-censorship is especially common in rural Ethiopia, where mobile phone coverage and access to the Internet is very limited. The main mode of government control is through extensive networks of informants and a grassroots system of surveillance. This rural legacy means that many rural Ethiopians view mobile phones and other telecommunications technologies as just another tool to monitor them, Human Rights Watch found.
“As Ethiopia’s telecom system grows, there is an increasing need to ensure that proper legal protections are followed and that security officials don’t have unfettered access to people’s private communications,” Ganesan said. “Adoption of Internet and mobile technologies should support democracy, facilitating the spread of ideas and opinions and access to information, rather than being used to stifle people’s rights.”
Source. ECADEF

ደቡብ ሱዳን ከግብፅ ጋር ወታደራዊ ትብብር መፈራረሟ አነጋጋሪ ሆኗል

የደቡብ ሱዳን መንግሥት ባለፈው እሑድ ከግብፅ ጋር የወታደራዊ ትብብር ስምምነት መፈጸሙን ‘ሱዳን ትሪቡን’ በሰኞ እትሙ ዘገበ፡፡ የኢትዮጵያ ‘ወዳጅ’፣ የግብፅ ደግሞ ‘ጠላት’ ተደርጋ የምትታሰበው ደቡብ ሱዳን ድርጊት አነጋጋሪ ሆኗል፡፡
የደቡብ ሱዳን መንግሥታዊ ቴሌቪዥንን ዋቢ አድርጎ እንደተጻፈው ዘገባ ከሆነ፣ አዲሱ ስምምነት የተፈጸመው በመከላከያ ሚኒስትሩ ኩዎል ማን ያንግ ጁክ የሚመራ የደቡብ ሱዳን ልዑካን ቡድን በካይሮ ጉብኝት ካደረገ በኋላ ነው፡፡ 
ከመከላከያ ሚኒስትሩ ጁክ በተጨማሪ የልዑካን ቡድኑ ከብሔራዊ ደኅንነት ሚኒስትሩ ከጄኔራል ማቡቶ ማሙር ማቴ፣ ከወታደራዊ ደኅንነት ምክትል ዳይሬክተሩና በግብፅ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር የተውጣጣ እንደሆነ ዘገባው ጠቁሟል፡፡
የደቡብ ሱዳን መከላከያ ሚኒስትር ከግብፅ ፕሬዚዳንት አዲል መንሱር ጋር በተገናኙበት ወቅት ግብፅ በደቡብ ሱዳን እያደረገች ያለችው ትብብርና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለአገሪቱ ግንኙነት መጠናከር አስተዋጽኦ ማድረጉን በመጥቀስ፣ ለግብፅ ምሥጋና ማቅረባቸውም ተገልጿል፡፡ ጁክ አክለውም የሁለቱን አገሮች ሕዝቦች የጋራ ጥቅምን በተመለከተ የግብፅ ወሳኝ አጋር ለመሆን ደቡብ ሱዳን ያላትን ቁርጠኝነት ለግብፅ ባሥልጣናት ማረጋገጫ መስጠታቸውም ዘገባው ያመለክታል፡፡
የግብፅ ፕሬዚዳንት አዲል መንሱር በበኩላቸው፣ የደቡብ ሱዳንና የግብፅ መንግሥታት በጋራ ለሚያከናውኗቸው ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች መንግሥታቸው ገቢ ማግኛ መንገዶችን ለማፈላለግ ያለውን ቁርጠኝነት እንደገለጹም ተጠቁሟል፡፡
በዘገባው የወታደራዊ ትብብር ስምምነቱ ዝርዝር ጉዳዮች ያልተገለጹ ቢሆንም፣ ምንጮች ግን ወታደራዊ ኤክስፐርቶችን በጋራ የመጠቀም፣ ልዩ ኃይሎችን የማሠልጠንና ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በጋራ መሳተፍን እንደሚያካትት መግለጻቸውን ዘግቧል፡፡
የግብፅ ወታደራዊ ኃይሎች በደቡብ ሱዳን እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ያመቻቻል የተባለው ይህ ስምምነት፣ ለኢትዮጵያ የብሔራዊ ደኅንነት ከፍተኛ ሥጋት ይፈጥራል እየተባለ ነው፡፡ ግብፅ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኢትዮጵያ የታላቁ ህዳሴ ግድብን ግንባታ እንድታቋርጥ ለማድረግ በተከታታይ እያደረገች ያለው ጫና አንድ አካል ተደርጎም ተወስዷል፡፡
ደቡብ ሱዳን የዓባይ የትብብር ስምምነት ማዕቀፍ (ሲኤፍኤ) እንድትፈርም ለማድረግ የማግባባት ሥራ እየሠራች ላለችው ኢትዮጵያ፣ ይህ ዜና ጥሩ ስሜት እንደማይፈጥርላት ተንታኞች በመግለጽ ላይ ይገኛሉ፡፡ ደቡብ ሱዳን ከሱዳን ነፃነቷን እ.ኤ.አ. በ2011 እንድትቀዳጅ ኢትዮጵያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተች ቢሆንም፣ በቅርቡ በደቡብ ሱዳን የተከሰተው የፖለቲካ ቀውስና ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር እያጠናከረች ከመጣችው ግንኙነት ጋር ተዳምሮ ለግብፅ ክፍተት እንደፈጠረላት የአፍሪካ ቀንድ የፖለቲካ ተንታኞች ያመለክታሉ፡፡
የአፍሪካ የደኅንነት ጥናት ተቋም ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር ሰለሞን አየለ የደቡብ ሱዳንና የግብፅ ስምምነት ዝርዝር ጉዳዮች ግልጽ ባይሆኑም፣ የተለያዩ መረጃዎች ግን ‘ቀላል’ (Soft) ሊባል የሚችል ይዘት እንዳለው እንደሚጠቁሙ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ስምምነቱ ሥልጠናና የባለሙያዎች ልውውጥ ላይ ማተኮሩ ለዚህ እንደ ማስረጃ ሊቀርብ እንደሚችል ያመላከቱት ዶ/ር ሰለሞን፣ ስምምነቱ በርካታ ጥያቄዎችን የሚያስነሳ ቢሆንም በኢትዮጵያ ላይ ስለሚያስከትለው ተፅዕኖ ለመናገር ግን ጊዜው ገና መሆኑን ይናገራሉ፡፡
ስምምነቱ ሊያስነሳ ከሚችላቸው ጥያቄዎች መካከል ኢትዮጵያ በደቡብ ሱዳን  ስትጫወተው የነበረውን ከፍተኛ ሊባል የሚችል ሚና ሊያዳክም ይችላል ወይ? ኢትዮጵያ በደቡብ ሱዳን የተከሰተውን የእርሰ በርስ ጦርነት ለማስቆምና የፖለቲካ ቀውሱን ለማረጋጋት እየሠራች ያለችው ሥራ ወዴት ያመራል? የሚሉት ወሳኝ መሆናቸውን ዶ/ር ሰለሞን አፅንኦት ሰጥተው ያስረዳሉ፡፡
‹‹ጉዳዩ ሊያሳስብ የሚችለው ኢትዮጵያን ብቻ አይደለም፤›› ያሉት ዶ/ር ሰለሞን፣ ሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር አፅንኦት ሰጥተው ሊከታተሉት እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡ ‹‹ከዚህ ያለፈ እንቅስቃሴ የሚያስፈልግ አይመስለኝም፡፡ የሚያስፈልግም ከሆነም ዲፕሎማሲያዊ ጫና በመፍጠር ከደቡብ ሱዳን ባለሥልጣናት ጋር መነጋገር ነው፤›› በማለትም ዶ/ር ሰለሞን አክለዋል፡፡
ዶ/ር ሰለሞን የስምምነቱ ተፅዕኖ ቀላል መሆኑ የሚያቆመው የግብፅ ወታደሮች ወደ ሱዳን በመግባት ከሁለቱ ወገኖች አንዱን የሚረዱ ከሆነና ወታደራዊ ሠፈር (Base) የሚያገኙ ከሆነ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ ስምምነቱ በግልጽ እነዚህን ተጨባጭ የሆኑ አሉታዊ አንድምታዎች በግልጽ የሚያሳይ ባይሆንም፣ ግብፅና ኤርትራ የደቡብ ሱዳን መንግሥት ፕሬዚዳንት ተቃዋሚ ለሆኑት ለሪክ ማቻር ይረዳሉ የሚለውን ሐሜት እውነት ሆኖ እሱን ለመቀልበስ አለመፈጸሙን ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ ከሪፖርተር ጥያቄ የቀረበላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የኢትዮጵያ መንግሥት ጉዳዩን እያጤነው እንደሆነ ገልጸው፣ በጉዳዩ ላይ ለጊዜው ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡