søndag 26. april 2015

ደህንነቶች የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ከፓርቲያቸው እንዲለቁ ጫና እያደረጉ ነው




መንግስት አይ ኤስ አይ ኤስ በኢትዮጵያውያውያን ላይ የፈፀመውን የጭካኔ እርምጃ ለመቃውም በጠራው ሰልፍ ላይ ተይዘው የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ከፓርቲው እንዲለቁ ደህንነቶች ጫና እያደረጉ መሆኑ ታወቀ፡፡ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ እስር ቤቶች ታስረው የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን ደህንነቶች ከፓርቲያቸው እንዲለቁ ጫና እያደረጉ እንደሆነና ከፓርቲው ከለቀቁ እንደሚፈቷቸው መግለጻቸው ታውቋል፡፡
በተለይ ካሳንቺስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙትን ወይንሸት ሞላንና ዳንኤል ተስፋዬን ሌሊት ሌሊት ከታስሩበት በማስወጣት ለረዥም ሰዓት ከታሰሩበት ጉዳይ ጋር የማይገናኝ ከፍተኛ ምርመራ እንደሚያደርጉባቸውና ከፓርቲው ካልለቀቁ በስተቀር እንደማይፈቱ እንደሚያስፈራሩዋቸው ተገልጾአል፡፡ በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ የሚደረገው አብዛኛው ምርመራ ፍርድ ቤት ላይ ፖሊስ ካቀረበባቸው ‹‹ሁከትና ብጥብጥ›› ክስ ጋር የማይገናኝና በፓርቲው ውስጣዊ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ነው ተብሏል፡፡
በሌላ በኩል በሰልፉ ወቅት ታፍሰው ከታሰሩት መካከል የሰማያዊ ፓርቲ አባል ያልሆኑትን ‹‹የሰማያዊ ፓርቲ አባል ነኝ፡፡ ፓርቲው ብጥብጥ እንዳስነሳ ልኮኝ ነው ወደ ሰልፉ የመጣሁት›› ብለው እንዲፈርሙ እያስገደዱ መሆኑን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ በርካታ የገዥው ፓርቲ አባላትም በአፈሳው ወቅት ተይዘው የታሰሩ ሲሆን አብዛኛዎቹ ከቀበሌ የምስክር ደብዳቤ አምጥተው መለቀቃቸውን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

torsdag 23. april 2015

የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያቀረቡት አስቸኳይ ጥሪ

April 23,2015
የተከበራችሁ ወገኖቼ፤ ከሰላሳ በላይ የሆኑ ወገኖቻችን አይ ሲስ በተሰኘ ህሊና ቢስ፣ ፀረ-ሰው እና ፀረ-ስልጣኔ ቡድን በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ የመገደላቸው መርዶ ከትናንት ወዲያ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓም ደርሶን ኢትዮጵያዊያን በያለንበት በመሪር ሀዘን ውስጥ ነን። ዛሬ “እግዜር ያጥናህ” ወይም “እግዜር ያጥናሽ” የሚባል ሰው የለም። ሁላችንም ሀዘንተኞች ነን። ካጣናቸው ቁጥራቸው በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ወገኖቻችን አሁንም በአራዶች መዳፍ ውስጥ መሆናቸው ሀዘናችን እጅግ የበረታ ያደረገዋል። ቁጥራቸው በትክክል የማይታወቅ ሆኖም በሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ዛሬም ሊቢያ ውስጥ ናቸው። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሁንም ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ናቸው። ሌሎች በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ደግሞ በየመን ከሰማይም ከምድርም በቦንብና በጥይት እየተማገዱ ነው።
ለምንድነው ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እሳት ውስጥ ለመማገድ የምንደፍረው? መልሱ ግልጽ ነው። አገር ውስጥ ተስፋ የለም፤ ወያኔዎች ተስፋችንን አጨለሙት። ከሳዉዲ በመከራ የተመለሱ ወንድሞቻችን ናቸው በሊቢያ በኩል ለመሰደድ ሲሞክሩ በአይ ሲስ ተይዘው የታረዱት። ወያኔዎች አገራችንና ክብራችን ዘረፉን። ወያኔዎች ስብዕናችንን ገፈፉን።
የዘመኑ ጥቂት የህወሓት ቱጃሮች ፎቆችን እየገነቡ በነሱ መጥገብ እኛ እንድናገሳላቸው ይፈልጋሉ። የኢትዮጵያ ሕዝብ መራቡ፣ መታረዙ፣ መደህየቱ እውነት ነው፤ ሆኖም ግን “ተራብኩ”፣ “ታረዝኩ”፣ “ደኸየሁ” ብሎ መናገር አይችልም። እውነት መናገር ያስቀጣል፣ ያስወነጅላል። በፍርደ ገምድል ችሎት እውነት መናገር “ሽብርተኛ” ያስብላል። እስር ቤቶችን የተሞሉት ለእውነት፣ ለፍትህ፣ ለነፃናትና ለእኩልነት በቆሙ ሰዎች አይደለምን?
በአይ ሲስ ያሳረደን ማነው? መልሱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ ነው። ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው። እንደ አገርና እንደ ሕዝብ የደረሰብን ውርደት የትም ብንሄድ የምናመልጠው አልሆነም። በአገር ውስጥ የደረሰብንን ውርደት ለማምለጥ ስንሰደድ ውርደት ተከትሎን ይመጣል።
ወገኖቼ፤ ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ የተሻለች አገር ሊኖረን አይችልም። ዛሬ የመሸሻ ጊዜ አይደለም። አገራችንን ከወያኔ ነጥቀን፤ በአገራችን ኮርተን በሰላም መኖር እንሻለን። ይህ መብታችን ነው። አገራችን የኛ ነች። አገራችን የጥቂት ወያኔዎች መፈንጫ አይደለችም።
ወገኔ፤ ዛሬ ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም በአርበኖች ግንቦት 7 ስም የማደርግልህ ጥሪ አድምጠኝ። በሀይማኖት፣ በብሔር፣ በጾታ ልዩነት ሳታደርግ ዛሬ በአንድነት እንደተሳህ አንድነትህን እንደጠበቅህ ቀጥል። አንድነትህን ለመሸርሸር ወያኔ የማይፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም፤ ለወያኔ ዱለታ ጆሮህን አትስጥ። የወያኔ አገዛዝ እንዲያበቃ በአንድነት ተነስ። ዛሬ የጀመርከው ትግል እዳር ሳይደርስ እረፍት የለንም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር በመጣመር የአገር አድን ኃይል የመገንባት ሥራውን እያጠናቀቀ ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት ሳንከፋፈል፤ ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ባካተተ ስብስብ ውስጥ አብረን ህወሓትን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የአንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ነው። የትግሉም የአገሪቷም ባለቤት አንተ ነህ። ስለሆነም ተነስ! “እንቢኝ” በል። ዘርፈ ብዙ የትግል ስልቶችን በመጠቀም ወያኔን አዳክም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! በትግልህ ፍሬ የአገርህ ባለቤት ሁን።
የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ሆይ!እናንተ የሕዝብ አካላት ናችሁ። የደረሰብንን ብሔራዊ ውርደት እያያችሁ፤ እሮሮዓችን እየሰማችሁ በሕዝብ ላይ መተኮስ በራሳችሁ ጭንቅላት ላይ መተኮስ ማለት መሆኑን ለደቂቃ እንኳን አትዘንጉ። ይልቁኑ ዛሬውኑ ነፃነትና ፍትህ ከጠማው ወገናችሁ ጎን ቁሙ።
የኢትዮጵያ ወጣቶች፤ የወጣትነት የፈጠራ ችሎቻችሁ መፈተኛው አሁን ነው። ለእያንዳንዱ ጥቃቅን ጉዳይ መመሪያ እስኪሰጣችሁ አትጠብቁ። እያሰላችሁ፣ እያጠናችሁ፣ እያደባችሁ፣ ወያኔን ታገሉ።
የታፈረች፣ የተከበረችና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናደርጋለን።
ብርሀኑ ነጋ
የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር
ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም

tirsdag 21. april 2015

የወያኔው ካድሬ ሬድዋን ሁሴን በሊቢያ የታረዱ ወገኖቻችንን አስመልክቶ የሰጠው የንቀት አስተያየት!!

ዲቦራ ለማ/ ኖርዌ

በሀገራችን ኢትዮጵያ ላለፉት 24 አመታት የህዝብን ጫንቃ አጉብጦ ህዝብን በዘርና በጎሳ ከፋፍሎ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለወገኖቻቸው ብቻ በማቀራመት ሀገሪቷን የጥቂት ጎጠኛ ወንበደዎች አድርገው እንደ ግል ንብረታቸው ሲቆጣጠሩዋትና ሲገዝዋት እንደነበሩ ለሁላችንም ግልፅ ነው። የሆነው ሆኖ ይሄ ሳያንሳቸው በዛው ልክ እነርሱ ወደ ላይ ኢኮኖሚያቸው እያደገ የሌላ የተማረው ህብረተሰብ ልጆቹን እንኳን በትክክል መመገብ የማይችልበት ደረጃ ደርሶ ዜጎች በፓለቲካ አመለካከታቸው በገዛ ሀገራቸው እንዳይኖሩ ለስደት መዳረግ ከጀመሩ አራት አስርተ አመታት ተቆጥረዋል።

ኢትዮጵያዊያኖች ከሀገራችን ተሰደን በተለያየ አለም ውስጥ የምንገኝ ቢሆንም የሚደርስብን ችግር እንደያለንበት አካባቢ መልኩን ይቀያይር እንጂ ችግሩ እንዳለ ቢሆንም በተይ በየመን፣ በሊቢያ፣ በሱዳ በአጠቃላይ በየአረብ ሀገራቱ እየደረሰ ያለውን ግፍ ግን በምንም አይነት ሚዛን ብናስቀምጠው የሚወዳደረው አይገኝም። አሁን ግን ይህንን ላወራ ሳይሆን በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ በወገኖቻችን ላይ የደረሰው አደጋ እጅግ አስደንጋጭና አሳዛኝ ነበር። ይህንን አይነቱ የጭካኔ ስራ ከሰው የተፈጠረ ሰው በእውነት ይህንን ያደርገዋል ብሎ ለማሰብ ከባድ ቢሆንም በወገኖቻችን ላይ ግን ተፈፅሞ አይተናል። 

ይህኛውን አዝነን ሳንጨርስ ISIS የተባለው የአሸባሪ ድርጅት ወደ 28 የሚሆኑ ወገኖቻችንን በሊቢያ በሚዘገንን ሁኔታ መግደሉን የውጪ ሚዲያዎች በፎቶ የተደገፉ ዘገባዎችን አድርሰውን ልባችን ተሰብርዋል። የበለጠ የሚያሳዝነው ዜጎቻችን መሞታቸው እየታወቀ ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን አላረጋገጥንም በማለት የሟቾች ቤተሰብ ሀዘናቸውን ተቀምጠው የብሄራዊ ሀዘን ቀን ማወጁ ቀርቶ ቢያንስ እግዜር ያፅናችሁ ብሎ በሚዲያ ለመናገር እኳን ጊዜ ፈጀቶባቸው ምንም አይነት የተቃውሞ መግለጫ እንኳን ሳያወጡ ሌሎች ሀገራት የሃዘን መግለጫዎቻቸውን ሲያቀርቡ ሰማን።

ከሁሉ የገረመኝ ግን አቶ ሬዲዋን ሁሴን በዚህ ጉዳይ ላይ ተጠይቀው ሌሎች ለሚሰደደዱ ሰዎች ትምህርት ይሆናል ብለው አረፉት አሁን ይሄ ሊያሳዝናቸውና ሊያስቆጫቸው ሲገባ እንደመቀጣጫ ይሆን ዘንድ ብለው የሰጡት አስተያየት እጅግ በጣም ውስጤን አስቆጣው እንደው ለመሆኑ እነኚህ የወያኔ ካድሬዎች ከሰው አልተፈጠሩም  ነግ በኔ ነው ለራሳቸው ቢያስቡ ጥሩ ነው። የካድሬው ሬድዋን  አስተያየት ይህን ይመስላል። ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ከታች ይጫኑ።

In Ethiopia, government spokesman Redwan Hussein said officials were in contact with its embassy in Cairo to verify the video's authenticity. Hussein said he believed those killed likely were Ethiopian migrants hoping to reach Europe. Libya has become a hub for migrants across Africa hoping to cross the Mediterranean to enter Europe for work and better lives.
"If this is confirmed, it will be a warning to people who wish to risk and travel to Europe though the dangerous route," Hussein said.

እግዚአብሄር ለሟች ቤተሰቦች መፅናናቱን ይስጥልን ሀገራችንንም ከጨካኝ የወያኔዎች እጅ ፈንቅሎ ያውጣልን። ወገን ሀገራችን ከፍተኛ የብሄራዊ ውርደት በየአቅጣጫ እየደረሰባት ነው የህዝባችንን እምባ ማበስ የምንችለው እኛው እራሳችን አንድ በመሆንና በመተባበር እንዲሁም ህይወታቸውን ሰጥተው ሀገራቸውን ነፃ ለማውጣት በሁለገብ ትግል በረሃ የወረዱ ወገኖቻችንን በማገዝ ትግሉን እናግዝ እያልኩ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።

ድል ለጭቁኑ ኢትዮጵያ ህዝብ!!

fredag 17. april 2015

ከራሳችን ውጪ ለችግራችን ደራሽ መንግስት የለንም! (በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ)


April 17, 2015
የኢትዮጵያውያን የውርደት ዘመን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ሰሞኑን ከተከሰተው እጅግ አስከፊ ሁኔታ ላይ አድርሶናል፡፡ የመን ውስጥ በተከሰተው ጦርነት ተጎጂ የሆኑትን የውጭ ዜጎች መንግስታቶቻቸው ቀድመው ሲያስወጡ ለኢትዮጵያውያን ግን የሚደርስላቸው አልተገኘም፡፡ ይህንን ውርደትም ወገኖቻችን ‹‹የመን ውስጥ የቀረነው እኛና ውሻ ብቻ ነን፡፡›› ሲሉ እጅግ በሚያሳዝን መልኩ ገልጸውታል፡፡ ኢትዮጵያውያን ላይ የመድፍ፣ የሞርታርና የአውሮፕላን ድብደባ ሲዘንብባቸው በመከራ ላይ ያሉት ኢትዮጵያውያን ስልክ እንዲደውሉ በፌስ ቡክ ላይ በመለጠፍ ከማላገጥ ውጭ ምንም ያላደረገው የህዝብ ስልጣንን በሀይል የተቆጣጠርው ገዥው ፓርቲ ለራሱ ስልጣን ይጠቅሙኛል ያላቸውን የጦርነቱ ተሳታፊዎች ደግፎ መግለጫ ሲሰጥ የኢትዮጵያውያንን ስቃይ እጥፍ ድርብ አድርጎታል፡፡ በአጭሩ ኢህአዴግ ለራሱ ጥቅም ሲል ብቻ በማያገባውና በማይወጣው ዓለም አቀፍ ጦርነት ውስጥ ሀገራችንን ሲዘፍቅ ጦርነቱን ያወጀው የሚደርስላቸው ባጡ ምስኪን ኢትዮጵያውያንና በኢትዮጵያ ላይ ነው፡፡ ይህም የሀገራችን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ከመቸውም ጊዜ በላይ የወደቀና ለዜጎች እንደማይቆም በድጋሚ ገሃድ የወጣበት ነው፡፡Semayawi party to welcome Andinet members
በየመን የተከሰተውን መርዶ ሰምተን ሳንውል ሳናድር ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በኢትዮጵያውያን ላይ ሌላ አስደንጋጭ አደጋና እና ሰቆቃ ልንሰማ ተገደናል፡፡ ኢትዮጵያውያን ሀብትና ንብረታቸው መዘረፉ ሳያንስ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው ሲያልፍ በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ተከታትለናል፡፡ የዚህ አሰቃቂ አደጋ ሰለባ የሆኑ የሌሎች ሀገራት ዜጎች በቶሎ ከደቡብ አፍሪካ ሲወጡ፣ እንዲሁም ሀገራቱ ዜጎቻቸውን መታደግ ያስችላል ያሉትን መፍትሄዎች ሲያስቀምጡ እና ሲያስጠነቅቁ ቢደመጥም ኢህአዴግ ግን እንደተለመደው የኢትዮጵያውያንን ሰቆቃና ስቃይ ከምንም እንዳልቆጠረው በግልፅ እየታየ ነው፡፡
በእርግጥ ላለፉት 24 ዓመታት ኢህአዴግ ሀገር ውስጥ የሚኖሩትን ዜጎች ሲያሰቃይ፣ በውጭ የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያንም የሆነ ያልሆነ ስም እየለጠፈ በጠላትነት ሲፈርጃቸው እንደቆየ አይተናል፡፡ ከኢትዮጵያውያን ይልቅ የራሱን የግል ጥቅም ሲያሳድድም ቆይቷል፡፡ በቅርቡ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ወገኖቻችን ከፍተኛ በደል ሲደርስባቸው ይህ ነው የሚባል እገዛ ያላደረገው ኢህአዴግ ሰማያዊ ፓርቲ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን በደል በማውገዝ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኘው የሳውዲ ኤምባሲ ላይ ተገኝቶ ሲቃወም የሳውዲ ፖሊሶች ሀገራቸው ውስጥ ኢትዮጵያውያን ላይ ከፈፀሙት በደል ያልተናነሰ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሰልፍ በወጡት ኢትዮጵያውያን ላይ በጭካኔ ድብደባ ፈፅሟል፡፡ ይህም ኢህአዴግ ለኢትዮጵያውያን የቆመ ሳይሆን በበእድ አገራት በኢትዮጵያውያን ላይ በደል ከሚፈፅሙት ያልተናነሰ ጨካኝ ስርዓት መሆኑን ያሳየበት ነው፡፡
ኢህአዴግ ለስሙ ‹‹የዳያስፖራ ፎረም›› በሚል የራሱን ደጋፊዎች አደራጅቶ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ለልማት የበኩላቸውን እንዲያደርጉ እየሰራ እንደሚገኝ በስሩ በያዛቸው ሚዲያዎች ሲያሰራጭ ከርሟል፡፡ ከዚህም ባሻገር ኢትዮጵያውያኑ ለእነሱና ለሀገራቸው እንደማያስብ በመረዳታቸው ምክንያት ፊታቸውን ስላዞሩበት ውጤታማ አልሆነም እንጅ በተለያዩ አገራት እየተዘዋወረ ለአባይ ግድብ የበኩላቸውን እንዲያዋጡ ሲወተውት ታይቷል፡፡ ሳንቲም ለመልቀም በተለያዩ የዓለም ከተሞች እየዞረ ኢትዮጵያውያንን የሚሰበስበው ገዥው ፓርቲ በችግራቸው ወቅት ግን ምንም አይነት እርዳታ ሲያደርግ አይስተዋልም፡፡ ይብሱንም ችግር ላይ ባሉት ኢትዮጵያውያን ላይ ሌላ በደል ሲፈጽምና በስቃያቸው ላይ የማላገጥ ያህል ፕሮፖጋንዳ ሲሰራባቸው እያየን ነው፡፡ ይህም የሚያሳየው ገዥው ፓርቲ ኢትዮጵያውያንን አባብሎ ገንዘብ ከመቀበል ያለፈ ለውድ ህይወታቸው ደንታ እንደሌለው ነው፡፡
በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሱ ባሉት ተደጋጋሚ ግፎች ተሸፈነ እንጅ ሰሞኑን ሌላ ኢህአዴግ ለዜጎች እንደማይጨነቅ የታየበት ክስተት እየተፈፀመ እንደሆነ በተለያዩ ድህረ ገጾች ላይ ለመከታተል ችለናል፡፡ ኢህአዴግ ለራሱ ጥቅም ሲል ለሱዳን መንግስት አሳልፎ በሰጠው ሰፊና ለም የሀገራችን ሉዓላዊ መሬት አካባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ሌላ አሳፋሪ እና አሰቃቂ ወንጀል እንደተፈፀመ ተዘግቧል፡፡ የሱዳን መንግስት ወታደሮች ድንበሩን ጥሰው የሱዳን አዋሳኝ በሆነው የሰሜን ጎንደር ዞን ጠረፋማ ቦታዎች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች ላይ ጥቃት ሲፈፅሙ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ሊታደጋቸው አልቻለም፡፡
ሰሞኑን በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው ሰቆቃ ኢትዮጵያውያን አገራቸው ውስጥ ቢሆኑም ቢሰደዱም ከመከራው ሊላቀቁ እንዳልቻሉ አመላካች ነው፡፡ በውጭም ሆነ በሀገር ቤት የሚኖሩ የአንድ ሀገር ዜገች መብታቸውና ክብራቸው ሊጠበቅ የሚችለው ሀገር ውስጥ ለሀገርና ዜጎች የሚያስብና የሚቆረቆር መንግስት ሲኖር ነው፡፡ ሆኖም ኢትዮጵያውያን የሚገዙት ኢህአዴግን በመሰለ ለሀገርና ለህዝቡ ደንታ በሌለው ስርዓት በመሆኑ የሰሞኑ ሰቆቃ የሚገርም አይደለም፡፡ መቼውንም ኢህአዴግ የሀገርና የዜጎቹን መብትና ክብር ያስጠብቃል ብሎ መጠበቅም ዘበት ነው፡፡
ኢትዮጵያውያን የሀገራችንና የራሳችን ክብር እና ደህንነት ማስጠበቅ ካለብን መጀመሪያ ሀገራችን ላይ የሚገኘውን ስርዓት በፅኑ መታገል የግድ ይለናል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ምቹ አስተዳደር፣ ዴሞክራሲያዊና ለዜጎች የሚያስብ ስርዓት ቢኖር መጀመሪያውኑም ወገኖቻችን በገፍ ለአደጋ ወደሚጋለጡባቸው አካባቢዎች ባልተሰደዱ ነበር፡፡ በመሆኑም በቅድሚያ ክብራችንን ለማስመለስ የነፃነት ትግሉን አጠናክረን በመቀጠል፣ እንዲሁም በውጭ የምንገኝ ኢትዮጵያውያን ለጊዜውም ቢሆን ራሳችን ከአደጋ ለማዳን በተለያዩ ማህበራት ተደረጃቶ በመንቀሳቀስ ብሎም ስርዓቱ እስካለ ድረስ ችግሮቻችን እየተባባሱ እንጂ እየተቀረፉ እንደማይመጡ በመገንዘብ በሀገር ቤት ስርዓቱን ለመቀየር የሚደረገውን ሰላማዊ ትግል በማገዝ የችግራችንን ሁሉ መሰረት የሆነውን አምባገነናዊ አገዛዝ ለመለወጥ የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል፡፡ ክብራችንን ልናስመልስ የምንችለው ሀገራችን ውስጥ እንዳንኖር ያደረገንን ስርዓት ቀይረን አንድም በገዛ አገራችን መኖር ስንችል፣ አንድም በአደጋ ወቅት ሊደርስልን የሚችል ተቆርቋሪና ለዜጎች የሚያስብ መንግስት መመስረት ስንችል ብቻ መሆኑን ልንገነዘበው ይገባል፡፡
በአሁኑ ሰዓት በደቡብ አፍሪካ ሰቆቃ እየደረሰባቸው ያሉ ወገኖቻችንን ለመታደግ በዓለም ላይ ተበትናችሁ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በችግር ውስጥ ለወደቁት ወገኖቻችን አጋርነታችሁን በማሳየት ዓለማቀፍ የተቃውሞ ድምፃችሁን እንድታሰሙም ሰማያዊ ፓርቲ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ እልባት እንዲያገኝ ፓርቲያችን የበኩሉን ጥረት እያደረገ ሲሆን በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰውን በደል ለማስቆም አዲስ አበባ በሚገኘው የደቡብ አፍሪካ ኤምባሲ በኩል የራሱን ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ በሌላ በኩል የመን ውስጥና በሱዳን አዋሳኝ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ስርዓቱ ከባዕዳን ጋር ተባብሮ የሚፈፅመውን በደልም ለህዝብና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ በማጋለጥ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ መረጃዎችን እያሰባሰበ ይገኛል፡፡
በትግላችን የሀገራችንና የራሳችን ክብርና መብት እናስጠብቅ!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!
ሚያዝያ 9/2007 ዓ.ም

onsdag 8. april 2015

በ24ኛው ክፍለጦር ውስጥ የሚገኙ ወታደሮች ትጥቃቸውን እየሸጡ በመጥፋት ላይ ናቸው ተባለ

April 8,2015
ትህዲኤን እንደዘገበው በምዕራብ እዝ በ24ኛ ክ/ጦር ውስጥ የሚገኙ የገዢው ኢህአዴግ ጉጅሌ ወታደሮች በየወቅቱ መሳሪያቸውንና ትጥቃቸውን እየሸጡ በመጥፋት ላይ እንዳሉ ተገለፀ::

ትህዴን ከክፍለጦሩ ውስጥ ባገኘነው መረጃ መሰረት ሲል በዘገበው ዘገባው በምዕራብ እዝ 24ኛ ክ/ጦር የገዢው ኢህአደግ ጉጅሌ የሰራዊት አባላት በሚቀጠሩበት ወቅት በስርአቱ የሚገባላቸው ቃል ሰለማይተገበር ካላቸው የማህበራዊ ችግር የተነሳ መሳሪያዎቻቸውንና ትጥቃቸውን እየሸጡ በመጥፋት ላይ እንደሚገኙ ከገለፀ በኋላ። በተለይ ደግሞ የክፍለ ጦሩ አባላት 2ኛ ረጅመንት የሆኑት ሁለት ወታደሮች መጋቢት 20/ 2007 ዓ/ም ክፍላቸውን ትተው ዳንሻ አልፈው በጎንደር መንገድ በመሄድ ላይ እያሉ ለሲቪሉ ማህበረሰብ መሳሪያቸውንና ትጥቃቸውን ግዙን መሳፈሪያ አጥተናል እንዳሏቸው ሊታወቅ ተችሏል::

መረጃው በማከል እንዳስረዳው የክፍለ ጦሩ አዛዦች ለሰራዊቱ የማህበራዊ አገልግሎት ተብሎ የመጣውን ገንዘብ። ከታች እስከ ላይ ተሳስረው ለግል ጥቅማቸው እያዋሉት መሆናቸውን በሰራዊቱ ተገምግሞ ሲያበቃ። እስከ አሁን ድረስ ግን የተተገበረ ለውጥ እንደሌለ መረጃው ጨምሮ አስረድቷል ሲል ትህዴን ዘግቧል: