onsdag 31. august 2016

በር ዜና: በመተማና አምባጊዮርጊስ ከፍተኛ ውጊያ እየተደረገ ነው | መተማ ቤቶች እየተቃጠሉ ነው | ጦሩ እየከዳ ሕዝብን እየተቀላቀለ ነው

(ዘ-ሐበሻ) በመተማና በአምባጊዮርጊስ ከተሞች ከፍተኛ የሆነ ውጊያ እየተደረገ መሆኑ ተሰማ:: የትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት በአማራው ላይ የሞት ፍርድ ከፈረደና መከላከያ ሰራዊቱ በሕዝብ ላይ እርምጃ እንዲወስድ ከተፈረደ በኋላ የመንግስት ጦርም ሕዝብ ላይ መተኮስ ከጀመረ ወዲህ በመተማ ቤቶች በመቃጠል ላይ ናቸው::
ለዘ-ሐበሻ የሚደርሱ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በመተማና አምባጊዮርጊስ ሕዝብ ከትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች ጋር እየተዋጋ ሲሆን አንድ ኦራል ወታደራዊ ተሽከርካሪ ላይ ጥቃት ከመፈጸሙም በላይ በርካታ የአጋዚ ጦር አባላት ላይ ጉዳት መድረሱ ተሰምቷል::

በአምባጊዮርጊስ እስካሁን ታይተው የማይታወቁ ጸጉረ ልውጥ ሰራዊት ከሕዝብ ጋር እየተታኩሱ ሲሆን ከተማዋ የጦር አውድማ መምሰሏ ተሰምቷል::
በሌላ በኩል በአብራጅራር ከተማ በመቶዎች የሚቆጠሩ የመክላከያ ሰራዊት አባላት በሕዝባችን ላይ አንተኩስም በሚል ከነትጥቃቸው ከሕዝብ ጋር በመቀላቀል የትግራይ ነጻ አውጪ ሰራዊትን እየተዋጉት መሆኑም ተዘግቧል:: ለዘ-ሐበሻ ከየስፍራው የሚደርሱ የመከላከያ ሰራዊት ድምጾች እንደሚያስረዱት ከሆነ ከሰራዊቱ መካከል ሕዝቤ ላይ አልተኩስም በማለት በርካታ አባላቱ ዝህቡን እየተቀላቀለ ነው::
ከታች የባህርዳርን ውሎ የሚያሳየውን ቭድዮ ይመልከቱ



Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar