søndag 25. oktober 2015

የኢሳት 5ተኛ አመት በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ በተሳካ ሁኔታ ተካሄደ!


 ዲቦራ ለማ/ኖርዌ

አርቲስና አክቲቪስት ታማኝ በየነ እንዲሁም ታዋቂው የኢሳት ጋዜጠኛ አፈወርቅ አግደው በተገኙበት ኢሳት የተቋቋመበትን የአምስተኛ አመት በአል በደማቅ ሁኔታ በኦክቶበር 24፣ 2015 በኦስሎ ከተማ ተካሄደ። በዝግጅቱ ላይ ከተለያየ የኖርዌ ከተማዎች የመጡ በርካታ ታዳሚዎች ተገኝተውበታል።



ዝግጅቱ በኖርዌ የሚኖሩ ታዳጊዎች ኢሳት የተመለከተ ዝማሬ አቅርበው ታዳሚውን ያስደመሙ ሲሆን በመቀጠል በኖርዌ የኢሳት ኮሚቴ ሊቀመንበር የእንኳን ደህና መጣችሁና የመግቢያ ንግግር በማድረግ ፕሮግራሙን ጀምሯል። በመቀጠል የተለያዩ አዝናኝና አስተማሪ መጣጥፎችና ግጥሞች እንዲሁም አጭር ጭውት በዝግጅቱ ላይ ቀርቧል። ለገቢ ማሰባሰቢያው የሚውል የምግብና መጠጥ ሽያጭ፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች ሽያጭ እንዲሁም የትኬት ሽያጮች ተካሂዷል።

ጋዜጠኛ አፈወርቅ አግደው የሚያስደንቅ ስራውን በመድረክ ያቀረበ ሲሆን አርቲስት ታማኝ በየነም የተለያዩ መረጃዎችን ለህዝቡ አቅርቧል። የጨረታው ሰአት ሲደርስ ጨረታውን አርቲስት ታማኝ በየነ የመራ ሲሆን በጨረታው ላይ በርካታ ተሳታፊዎች ተሳትፈዋል። የጨረታውን ዋንጫ ያቀረቡት በኖርዌ በርገን ከተማ ነዋሪ የሆኑ የኢሳት ቤተሰቦች ሲሆኑ በመድረክላይም ኢሳት ይቀጥላል የሚል የራሳቸውን ዝማሬ አቅርበዋል።

ከጨረታ፣ ከምግብና መጠጥ ሽያጭ፣ እንዲሁም ከትኬት ሽያጭ እንዲሁም ከተለያዩ ነገሮች ሽያጭ ለኢሳት ከፍተኛ ገቢ ተገኝቷል። ዝግጅቱ በደማቅ ሁኔታ በኖርዌይ የሰአት አቆጣጠር ከምሽቱ 23፡00 ተጠናቋል።



ኢሳት በእኛ ድጋፍ ይቀጥላል!!

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar